Get Mystery Box with random crypto!

Saved by Grace✔️

የቴሌግራም ቻናል አርማ onlygraceonlyfaith — Saved by Grace✔️ S
የቴሌግራም ቻናል አርማ onlygraceonlyfaith — Saved by Grace✔️
የሰርጥ አድራሻ: @onlygraceonlyfaith
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 913
የሰርጥ መግለጫ

ዓላማችን የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሣፍር ሠራተኛ ሆኖ የተፈነውን ራሳችንን ለእግዚአብሔር ማቅረብ ነው።
ለአስተያየትዎ
@biniamsol

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-27 21:57:46
ከተአምራቶች ሁሉ የሚበልጥ ተአምር:-
''ድንግል ፀነሰች ፣ ወንድ ልጅም ወለደች'' ስሙም፣ ድንቅ መካር፣ ኀያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም ልዑል ፤ አማኑኤል ፣ #ኢየሱስ ይባላል።
78 viewsBiniam Solomon, edited  18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 14:11:29
እግዚአብሔር ሁለም አጁን ዘርግቶ እየጠበቃችሁ ነው ፣ ኑ ወደ እርሱ፣ እርሱ ለነፍሳችሁ ሕይወት እና እረፍትን ይሰጣል። ክርሰቶስ ለብዙዎች ኃጢአት መስቀል ላይ ተሰቅሏል ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት አለው። ጊዜው ነገ አይደለም ፣ ዛሬም አይደለም ፣ ጊዜው አሁን ነው። ሁሉ ሰላም ነው ስትሉ ክርስቶስ ዳግም በድንገት ከገለጠ መጨረሻቹ ሲኦል ይሆናል ፣ ከሞት በኃላ ንስሐ የለም። ከኃጢአታችሁ ልትመለሱና በክርስቶስ ልታምኑ ጊዜው አሁን ነው።

“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
@onlygraceonlyfaith
353 viewsBiniam Solomon, edited  11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 21:05:46
#በክርስቶስ_ብቻ
#መላእክቱንም_ስንፍና ይከስሳቸዋል(ኢዮብ 4፥18) ወደ እግዚአብሔር ሊያቀርቡን አይችሉም። ጻድቃንስ፦ እነርሱ የሰውን ድካም የሚረዱ ሰዎች ብቻ ሲሆኑ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የሚያስችላቸው ምንም የእግዚአብሔር አይነት ጽድቅ የላቸውም ፣ በራሳቸው ልክ እንደ እኛ ደካሞች ናቸው። “ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤”

መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል ወደ እግዚአብሔር ሊያቀበን የሚችለው ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ብቻ ነው ፣ በክርስቶስ መካከለኝነት ካልሆነ በቀር ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ማንም አይችልም ፣ ወደ አብ ሊያቀርባችሁ ኢየሱስ ይፈልጋል ወደ እርሱ ኑ የዘለለምን ሕይወት ታገኛላችሁ ፣ ወደ እርሱ ካልመጣችሁ ልትድኑ አትችሉም። ከኢየሱስ ውጭ ማንም ሊያድናችሁ አይችልም። “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።”
— ማቴዎስ 11፥28
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6
142 viewsBiniam Solomon, edited  18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 12:59:32 እንዲሆን ሞገስ ዘውዴ የአንገት . (1) .
ሁሌ ቃላህ ነውና የእግሬ መብራት
መንገዴን የሚያቀናልኝ በአንተው ስርዓት (2x)

አቤቱ እንዳልበድልህ ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
መንገድም እንዲነጻልኝ ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
በትዕዛዝህ መንገድ እንድሮጥ
ተንሸራትቼም እንዳልገባ ማጥ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
ስንፍናን ተግቼ ኃጢአትን ሳላምጥ
ሕይወቴ በድንገት እንዳያመልጥ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን

ስትተትን እንዳስተውላት ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
እንድሰወር ከስውር ኃጢአት ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
ከጓደኞቼ ጋር በሳቅ ጨዋታ
መስመር እንዳላልፍ እንዳልረሳ ጌታ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
የድፍረት ኃጢአት ጠፍሮ እንዳይዘኝ
ቃልህ ፍርሃት ሁልጊዜ እንዲያዘኝ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን

ቃልህ ይሁን ትዝታዬ ቃልህ ይሁን (2x)

መፅናናት ሲያስፈልገኝ ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
መከራው ሲያሳድደኝ ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
ከጠላቴ ዛቻ ከምክሩ እንዳልፈራ
ልቤ እንዲጠበቅ በምክር እንድመራ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
የኃጥአን ገመዶች ሲተበተቡብኝ
አለቆች ተቀምጠው ሲያሙኝ
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን

በአመፀኞች እንዳልቀና ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
የግፍ እንጀራ እንዳልበላ ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
. (2) . ኑሬ ቤቴን ለመሙላት
በከንፈሬ . (3) .
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን
እግሬ እንዲከለከል ከክፋት ጐዳና
በፈተና ሁሉ እምነቴ እንዲፀና
ትዝታዬ ቃልህ ይሁን

ቃልህ ይሁን ትዝታዬ ቃልህ ይሁን (2x)

ሕግህን እጽፈዋለሁ በልቦናዬ
እንዲሆን ሞገስ ዘውዴ የአንገት . (1) .
ሁሌ ቃላህ ነውና የእግሬ መብራት
መንገዴን የሚያቀናልኝ በአንተው ስርዓት (2x)
ቤቴሌሄም ተዘራ #4
144 viewsBiniam Solomon, 09:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 20:24:53 ከሞት በኃላ ንስሐ የለም ፣ የመጨረሻው እስትንፋስ ከተሳበ በኋላ መለወጥ የለም። በክርስቶስ ለማመን እና የዘላለምን ሕይወት የምንይዝበት ጊዜ አሁን ነው። ከጨለማ ወደ ብርሃን የምንመለስበት፣ ጥሪያችንንና ምርጫችንን የምናረጋግጥበት ጊዜ አሁን ነው።
159 viewsBiniam Solomon, 17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 20:01:11 #ተስፋ
በመጀመሪያ ተስፋ ማለታችን በዚህ ቁሳዊ ዓለም ምናልባት ልሆንም ላይሆንም ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው ተስፋ እንዳይደለ ልብ ማለት አለብን። ተስፋ ማለታችን ከማይዋሸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ለክርስቲያኖች እርሱ ራሱ ቃል በገባው መሠረት ወደ ፍት የሚያደርገው ነው። ይህ ተስፋ እርግጥና ጽኑ የሆነ ነው እንዲሁም የከበረና መልካም የሆነ ተስፋ ነው። እውነት ነው ተስፋችን የሆነውን የታረደልንን ያንን በግ ፊትለፍት እናየዋለን። እንዲሁም ከእርሱ ጋር ለዘላለም እንኖራለን።
አሜን
222 viewsBiniam Solomon, 17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 21:56:38
ብዙ በእንግሊዝኛ በተሰሩ አጫጭር ፍልሞች ሰዎችን ለማሳቅ ''Jesus'' የሚለውን ስም እንደመቀለጃ አድርገው ሲጠቀሙ ይስተዋላል ፣ እንዲሁም አገራችን በሚሰሩ ቀልዶች ''በኢየሱስ ስም'' በሚለው ስም አብዛኛውን ግዜ ሰዎችን ለማሳቅ መጠቀም ከጀመሩ ሰንበት በት ብሏል። እኛም አንዳንዴ የነዚህ በጌታ ስም ከምቀልዱት ጋር ተስማምተን ስምምም ብለናል። አሁን አሁን tik-tok ላይ የሚቀለዱ ቀልዶች በአብዛኛው በዚህ ስም በመቀለድ ነው።

አንድ ነገር የማውቀው አሁን ላሾፉበት ወደፍት በጌታ ፍት መልስ ይሰጣሉ ፣ ጉልበት ሁሉ ''ኢየሱስ'' ለምለው ስም ይሰግዳሉ። ለዚህ ስም የማይንበረከክ ፍጥረት አይኖርም ፣ አሁን ''እሱ ሰው ብቻ ነው'' ፣ አንዳንዱ ደግሞ ''ነብይ ብቻ ነው'' ብለው የሚያምኑ እንኳን ለእርሱ ተንበርክከው ይሰግዱለታል ፣ ወደተዘጋጀላቸው ስፍራም ይሄዳሉ።

''ኢየሱስ'' የከበረ ስም ነው።
306 viewsBiniam Solomon, edited  18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 15:55:15 #ወንጌል
ወንጌል ስለ ልጁ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም እርሱ ስለ ሠራው ሥራ ነው። ወንጌል ሙሉ ነው ፣ ቃል ሥጋ ስለመሆን ፣ ከድንጌል ስለመወለድ ፣ ስለ ኃጢአተኞች መሰቀል ፣ በሦስተኛው ቀን መነሳቱ እንዲሁም እንደገና በፍርድ እንደሚመለስ እኛን ክርስቲያኖችን ወደ ራሱ እንደሚሰበስብ የሚተርክ ነው። ወንጌል ተስፋ የለላቸው ኃጢአተኞች አምነው የሚድኑበት ፣ ከኃጢአታቸው ንስሐ የሚገቡበት ፣ እግዘብሔርን መፍራት የምንማርበት ፣ እንዲሁም ክርስቶስ ስለሚመሠርተው መንግሥት ነው ፣ ወንጌል ሙሉ ነው።
አሜን!
285 viewsBiniam Solomon, 12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 13:34:05 #Attention
ከማንም ጋር የግል ግጭት የለኝም ፣ አይኖረኝምም። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስን አጣመው ክርስቲያኖችን ወደ ጨለማ ሕይወት እንዲጓዙ ከሚያደርጉት ጋር ተስማምቼ መኖር ሆነ ዝም ማለት አልችልም።

እትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አከባቢዎች እንድሁም ሰሞኑን ወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ኮንፈረንስ(Conference) በማዘጋጀት ፣ ብዙ ክርስቲያኖችን በገንዘብ አታለው ክፉ ትምህርታቸውን እና ባእድ አምልኳቸውን በማሰራጨት ላይ የሚገኙ ራሳቸውን #Living_stream_ministry ብለው የሚጠሩ እንድትጠነቀቁ አሳስባለሁ።

ወንጌልን ለማያምኑ ሰዎች መስበክ አይፈልጉም ነገር ግን ከተለያዩ አብያተክርስቲያናት ክርስቲያኖችን ወደ ራሳቸው በመሳብ ላይ ይገኛሉ። በተለያዩ አካባቢ ያላችሁ የቃለ ሕይወት ፣ ሙሉ ወንጌል እንዲሁም የሁሉም አብያተክርስቲያናት መሪዎች ምዕመናኑ ከእነዚህ ሐሰተኛ ድርጅቶች እንዲቆጠቡ እንዲታሳስቡ እወዳለሁ።

እኔ ባለሁበት አከባብም(ሣውላ ከተማ) ለመጀመር እንዳሰቡ መረጃ ደርሶኛል ፣ እንዲሁም ቡልቅ ከተማ ራሳቸውን አደራጅተው እንደቆዩ እኔ እራሴ አይቻለሁ ፣ በተቻላችሁ አቅም የቤተክርስቲያን መርዎች እግዝአብሔር እንደ ባለአደራ ቤተክርስቲያንን ከሐሰተኞች እንድትጠብቁ መርጧችኃልና አደራችሁን እንድትወጡ አሳስባለሁ።

ክፉ የሆነ የሰይጣን ተልኳቸው የሚጀምረው ቤተክርስቲያንን በመበታተን ስለሆነ ፣ ቃለ ሕይወት ሙሉ ወንገል እንድሁም ከራሳቸው ውጭ ያሉት ሁሉ ቤተክርስቲያናት ሐሰተኛ ናቸው በማለት ይጀምራሉ ፣ ሥላሴን በመካድ ፣ መጽሐፍ ቅዱስ በአእምሮ ማጥናት አስፈላጊ አይደለም ቃሉን መብላት ነው በማለት እንዲሁም ሰው አምላክ ነው በማለት ክፉ አስተምሯቸው ይቀጥል ፣ ''oh lord jesus' ፣ አንተን እንደ ምግብ እንበላለን ፣ እንደ ጁስ እንጠጣለን ፣ እንደ ጀላት እንመጥጣለን ፣ እንደ ልብስ እንለብሳለን'' በሚሉ መልካም መስሎ በሚታዩ ቃላት ባእድ አምልኳቸው ይጀምራሉ ፣ ቀስ በቀስ አምላክ ነህ ፣ ዊትኔስ ሊ አባታችን ነው በማለት እሱ የጻፋቸውን ጹፎች ከመጽሐፍ ቅዱስ እኩል ወደማየት ያመራሉ ፣ እንድሁም አንዳንዶች የእርሱ መጽሐፍ ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚበልጥ ያወራሉ።

በተለያዩ አከባቢ ያላችሁ ሁሉ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ድርጅት እንድትቆጥቡ እንድሁም Share በማድረግ ክርስቲያኖችን ከሐሰተኞች እንድትታደጉ እጠይቃችኋለሁ።
299 viewsBiniam Solomon, 10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 13:33:57
184 viewsBiniam Solomon, 10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ