2022-05-16 19:40:08
የከተማው ዳኞች አንዱ ወደ ፊት መጥቶ ቆመ "ስለ ወንጀል እና ቅጣት ንገረን"አለ
እሱም እንዲ መለሰለት ;በሌሎች ላይም ሆነ በራሳችሁ ላይ ክፉ ስራ የምትሰሩት መንፈሳችሁ በህዋው ውስጥ ሲዋልል ብቻችሁን ስትሆኑ እና ጠባቂ ሳይኖራችሁ ሲቀር ነው።ለዚያ ለተሰራው ሀጥያትም በቅዱሳን ደጅ ቆማቹ ማንም ሳያስተውላችሁ በሩን ማንኳኳት እና ለጥቂት ጊዜ መጠበቅ ይገባችኃል ። ምክኛቱም ህሊናቹ እንደ ውርቂያኖስ ነውና። ሳይረክስም ለዘላለም ይቆያል.....
ህሊና እንደ ሰማዩ ሁሉ ባለክንፎች ን ብቻ ከፍ አርጎ ያነሳል.....
ብዙውን ጊዜ ስለ አንድ በደልን የፈፀመ ሰው ስትናገሩ ሰውየው ከእናንተ አንዱ እንዳይደለ ይልቅስ ለእናንተ እንግዳ እና ወደ አለማቹ ዘው ብሎ የገባ ፍጡር እንደሆነ አድርጋቹ ስትናገሩ እሰማለሁ።እኔ ግን ቅዱሳንና ፃድቃንም እንኳን ቢሆኑ በእያንዳንዳች ውስጥ ካለው ከሁሉ ክፋዎችና ደካሞች በውስጣችሁ ካለው ከሁሉ ዝቅ ከሚለው የበለጠ ዝቅ ብለው ሊወድቁ እንደማይችሉ እነግራቸዋለሁ....
በተጨማሪ ከጠቅላላው ዛፍ እውቀት አንዲት ነጠላ ቅጠል ብቻዋን ወደ ቢጫነት እንደማትለወጥ ሁሉ ክፉ አድራጊውም ቢሆን የእናንተ ሁሉ ድብቅ ፍላጎት ሳይኖር ክፉ ሊሰራ አይችልም......
ልክ እንደ ሰልፈኞች አንድ ላይ ሆናችሁ ነው ወደ ህሊናችሁ የምትጓዙት።እናንተ መንገዱና የመንገዱ ተጓዦች ናችሁ.....
ከመሃላችሁ አንዳችሁ ቁልቁል ስትወድቁ የምትቸወድቁ ከኃላችሁ ላሉት ከሚንከባለለው ድንጋይ እንዲጠነቀቁ ነው...
አዎ የምትወድቁትም ከፊታችሁ ላሉትም ነው። ከፊታችሁ ያሉት ፈጣንና ተጠንቅቀው የሚራመዱ ቢሆንም የሚንከባለለውን ድንጋይ ከመንገዱ ላይ ሊያስወግዱት አልተቻላቸውምና ለነሱም ስትሉ ትወድቃላችሁ....
ምንም እንኳ ቃሉ ለልቦቻችሁ ቢከብዱም ይህን እነግራችኃለሁ ፦ተገዳዩ ለገዛ እራሱ መገደል ከኃላፊነት አያመልጥም
ተዘራፊው በመዘረፉ ከተወቃሽነት አይድንም
ፃድቅ የሆነውም ሰውም ከክፉ ተግባራት የነፃ አይሆንም
ከደሙ ንፁህ የሆነውንም ወንጀለኛው ካደረጋቸው አድራጎቶች የፀዳ አደለም ....
አዎን ብዙውን ጊዜ ጥፋተኛው የተበዳዩ ተጠቂ ነው።እንደዚያም ሆኖ በአብዛኛው ጥፋተኛ ተብሎ የተፈረደበት ላልተፈረደባቸው እና ተወቃሽ ያልሆኑትን ሰዎች ቀንበር ተሸካሚ ነው።እናም ንፁሁን ከኃጥያተኛው ደጉንም ከክፉው መለየት አይቻላችሁም....
ለምን ብትሉ ጥቁር እና ነጭ ክር በአንድነት ልብስ እንደሚሰራባቸው ሁሉ እነዚህም በፀሀይ ፊት አንድ ላይ ይቆማሉና።ጥቁር ክር ሲበጠስ ሸማኔው የሚመረምረው ጠቅላላውን ልብስ ነው። የሽመና መሳሪያዎቹንም ሳይቀር ይመረምራል .....
ከእናንተ ውስጥ ማነኛችሁም ለባሏ ታማኝ ያልሆነችን ሚስት ለፍርድ ሊያቀርባት ቢወድ የባሏንም ልብ በሚዛን ይመዝን ነፍሱንም በመለኪያ መሳሪያዎች ይለካ...
በዳይን በጅራፍ ሊገርፍ የተነሳሳም የተበዳዩን መንፈስ ይመርምር....
በስጋው ታማኝ በመንፈስ ሌባ ለሆነ ሰው ምን ፍርድ ትሰጡታላቹ?
በስጋው የሚያርድ በመንፈሱ ግን እርሱ ራሱ ለታረደውስ ምን ቅጣት ትጥሉበታላችሁ?
እናስ በተግባር አታላይ እና ጨቋኝ ቢሆንም እርሱ ራሱ የተጨቆነውን የተዋረደውንስ እንደምን ትዳኙታላችሁ?
ገና ሳይፈረድባቸው ፀፀታቸው ከመጥፎ ድርጊታቸው በእጅጉ በልጦ የተገኘውንስ እንዴት አድርጋችሁ ነው ቅጣት የምትጥሉባቸው?....
በአግባቡ እያገለገላችሁ የምትገኙት ያ ህግ በራሱ የሚሰጠው ፍታሀዊ ብይንስ ፀፀት አይደለምን?እንደዚያ ሆኖ በንፁሀን ላይ ፀፀት ልታሳድሩ ወይም ጥፋተኞች ልብ ላይ ፀፀት ነቅላችሁ ልታወጡ አይቻላችሁም። ሳይታዘዝ ከተፍ በሚለው ሌሊት ሰዎች ከእንቅልፋቸው ሊነቁና ራሳቸውን አተኩረው ሊመለከቱ ይችላሉና ...
ታድያ እናንተ የቀን ደማቅ ብርሀን ባለበት ሁሉንም ድርጊት ካልተመለከታችሁ በስተቀር እንዴት ፍትህን ልታውቁ ይቻላችኃል?...
አንድ ሰው ይቁምም ይውደቅ የምታውቁትስ በድንክዬ እሱነቱ አይደለምን?ደግሞስ የቤተመቅደስ የማዕዘን ድንጋይ መሰረት ከታችኛው ድንጋይ የበለጠ ከፍ ያለ ይሆናል...
የጠቢባን መንደር ከ ጀብራን ካህሊል
461 views16:40