2022-03-10 16:27:00
"ለወደድከው ሞተህ ለጠላኸው ካልኖርክ
እንኳን ልትፈጠር ገናም አልተጀመርክ "
(አያ ሙሌ "ሙሉጌታ ተስፋየ )
ሰው ስንሆን ቅፅበቶች ነን ።
ደስታችን ፣ ሀዘን ሳቅ ጨዋታችን ሁሉ ግዜያዊ ነው ዘላለምን መዝለቅ ሚችለው በጥበብ የተለወሰ ክዋኔና ከያኒ ብቻ ነው ። ከነዛ መሀል አንዱ ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋየ (አያ ሙሌ) ነው ። በዘመን ጉያ በነበረበት ጊዜ እሱነቱ ሳይገለጥ ወይ ግልጡን በዋሹ ዘመኔወች ታጅቦ ትላንቱን ቢያንቀላፋም ዘመን ቆጥሮ ከያኒውን በዚህ ወቅት የማያነሳ ፣ የማያወድስ ብዕርና ፀሀፊ የለም ። ትላንትን ሲያንቀላፋ ትቶ ከሄዳቸው ክንውኖቹ በተጨማሪ
" እንደሰው እስኪያልፍለት እንደምንም አስታውሱት
እንግዲህ ልጄን አደራ ሌላው ቢቀር ፊት አትንሱት
. .. .. "አደራ ልጄን . . . "
ተብሎ የተዜመለትን የአብራኩን ክፋይ ሸህ አብዱን (ዳንኤል ሙሉጌታን )
አደራ ትቶልን ሄዷል ነበር ። ታዲያ ይሄ ክፋዩ አደራን በዘነጋ ትውልድ በራሱ ትላንት ያለታዛቢ በዘመን አሮንቃ ሲላወስ ቢቆይም ዛሬ ላይ ከብዙ ውጣ ውረድ በሗላ በሊቀ ጠበብቱ አባቱ ሙሉጌታ ተስፋየ(አያ ሙሌ) ስም መሀል የጁ (ወልዲያ ላይ ) በቅርቡ የመፀሀፍ መሸጫና ማከራያ ስፍራ ሊመሰርት ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል ።
"አወይ እኔ መገን አወይ እኔ መገን
መላና ባላውን አጣነው ፈልገን
እንዲህ እሩቅ ነው ወይ አጥቢያና ወጋገን
ይቸግራል ለካስ ሀገር ይዞ ወገን
* ና መገና . . . መገና . . . መገና . . .*
በሚለው ባባቱ ትዝብት ውስጥ እንዳንወድቅ ዘንዳ ሁላችንም በምንችለው ሁሉ ሸህ አብዱን እናግዘው ዘንድ ከወዲሁ "አደራ . . . " ችንን እንውውጣ እንላለን ።
በመሆኑም ደሴና አካባቢዋ የምትገኙ ይህን መልካም ተግባር መደገፍ ምትፈልጉ ሁሉ ከዛሬው እለት አንስቶ የቻላችሁትን ያክል መጥሀፍ አልያም መሸመቻይቱን (ደሴ ከመርሆ ግቢ ቁልቁል ወደ መነሀሪያ በሚወስደው መንገድ ከቤተሰብ መምሪያ አደባባይ ሆናችሁ #ለሜሪ ጀማል በ09 23 75 13 54 ብላችሁ ብትደውሉ ስትበር መታ ትቀበላለች ።
አልያም...
መምጣት ለማትችሉት (ከደሴ ውጭ ላላችሁ) ደሞ
በ ስልክ ቁጥር 09 09 06 83 60 (መዲና ታደሰ)
09 53 81 20 20 (ሰለሀዲን አሊ )
09 85 15 78 78 (ቀልብ አልባው (አዩብ)
ብላችሁ ብትደውሉልን ያላችሁበት ድረስ ዘልቀን እንቀበላችኋለን ። በመልካም ተግባር ያያሙሌን ነፍስ እንዘክር ።
770 views13:27