Get Mystery Box with random crypto!

እናና እረኛ ፥ እሆናለሁ ፣ በግ ፥ እጠብቃለሁ ፣ ብለሽ ፥ እንዳልነበር ፣ በግ ፥ አበቃሽ | መጽሐፍ ቤት

እናና

እረኛ ፥ እሆናለሁ ፣
በግ ፥ እጠብቃለሁ ፣
ብለሽ ፥ እንዳልነበር ፣
በግ ፥ አበቃሽ ላፈር ?
እንዳብዬ ፥ አስተዋይ ፣
መቼም ፥ አይኔ ባያይ ፣
ፍቅር፥ ሲናፍቀን ፣
እንባ እንዴት፥ አያንቀን ?
ዘመን ቢጎል ካምናው ፥ ዘንድሮ ቢከፋም ፣
ሐገር ብትመነምን ፥ ደግሰው አይጠፋም ፣
ነብስ ንጹህ ስትሆን ፥ ትዘራለች ፍቅር ፣
እንኳን ደጉ ቀርቶ ፥ ክፉም ይላል ይቅር ፣
ቸርነት እምዬ ፥ እናንዬ አማራ ፣
መስለው እዬታዮኝ ፥ እምባዬ እንዴት ያብራ ፣
ጥጋቡ ይሉት በግ ፥ ወግቶኛል እያለች ፣
በባረቀ ሃሳብ ፥ ያች እንቡጥ ተቀጨች ፣
ባይለው ነው እንጂ ፥ ትረፊ ባይላት ፣
በጉ ወንፈል ያውቃል ፥ እንኳንስ ሊገላት ፣
ቀልብ የታጣ ጊዜ ፥ ሀገር ይታመማል ፣
የባረቀ እያለ ፥ እንዴት ቀንድ ይታማል ?
ወግ ጥሰው ቢንቋት ፥ አልፋለች ግዴለም ፣
ጫንቃዋ ያዘለው ፥ ጅራፍ ብቻ አይደለም ፣
እንዳረገው ፍቅር ፥ አብነትን ያ ደም ፣
ምናለ እውን ሆኖ ፥ ለሐገር ቢደገም !

እናና
ዳን አበባው ንጋቱ
ነሐሴ 2014 ዓ.ም