Get Mystery Box with random crypto!

➨ አለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር እግዚአብሔር በእኛ ላይ አላማ ነበረው። ➨ ወላጆቻችን ሳንወለድ | መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ

➨ አለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር እግዚአብሔር በእኛ ላይ አላማ ነበረው።
➨ ወላጆቻችን ሳንወለድ በእኛ ላይ አላማ ይኖራቸው ይሆናል። አላማቸው ግን ስሜን ያስጠሩልኛል የምል ይሆናል።

➨ እርሱ የህልውናና የስም መገኛ ነውና እጠፋለሁ ብሎ ስሙን እናስጠራ ዘንድ አልፈጠርንም።
ገና ህልውናና ስም ሳይጀመር ወደደን።
➨ ከመፈጠራችን በፊት የወደደን
ከመገኘታችን በፊት የመረጠን
ወላጆቻችን ሳያውቁን ያወቀን ወላጆቻችን ሳይወለዱ የወደደን ድንቅ አምላክ ነው።

➨ ወላጆቻችን ተወልደን ብያዩን ሳሱልን፣
እሱ ግን ደም ሳይረጋ አጥንት ሳይሰካ ከማኅፀን ህልውናችን ሳይጀመር ወደደን።
➨ ወላጆቻችን አድገን ቁም ነገራችንን መዝነው ወደዱን።
➨ እሱ ግን ገና ደግና ክፉ ሳንሰራ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር አፈቀረን።

➨ ከዓለም በፊት ወዶናልና ዓለም ሲያልፍም ይወደናል።
ከዘመን በፊት ወዶናልና ዘመን ሲታጠፍም ይወደናል።
ከዓለም በፊት ግዜ አልነበረም ➨ከጊዜ ውጪ ወዶናልና ፍቅሩ በግዜ የማያበቃ ዘላለማዊ ነው።

ጸጋ ይብዛላችሁ