ማስታወቂያ ስለ ኮርሱ ማብራሪያ የትምህርቱ ዋና ዓላማ ➺ የግእዝ ቋንቋን ተምረው ለማያውቁ ከጅማሬው ማሳወቅ እና ቋንቋውን መደበኛ በሆነ መልኩ ለመማር የሚፈልጉትን አነሣሥቶ ጥንታዊ የሆነ ቋንቋዎችን ለዘመኑ ሰዎች በዘመናዊና በቀላል አቀራረብ ማስተማር ነው። የትምህርቱ አሰጣጥ ➺ ኮርሱ መሠረታዊ የሆኑ ትምህርቶች የያዘ ሲሆን በ 4 ምዕራፎች ተከፋፍሎ ይሰጣል። የትምህርት ጊዜያት ከሰኞ እስከ ዓርብ ሲሆን ከንጋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ትምህርቶች ይለጠፋሉ። ስለዚህም በሚመችዎት ሰዓት ላይ ገብተው መከታተል ይችላሉ። ➺ ትምህርቶች የሚሰጡባቸው መንገዶች በጽሑፍ ፣ በድምፅ እና በቀጥታ ቮይስ ቻት (Voice Chat) ሲሆን አጠቃላይ ዘመኑን በዋጀ መልኩ ይሰጣል። በዚህም መሠረት በየዕለቱ ለጥቂት ደቂቃ ያክል (10-15) ሰጥተው ትምህርቱን ያካሂዳሉ ማለት ነው። ➺ ውይይቶች፣ መልመጃዎች፣ የቤት ሥራዎች እንዲሁም የምዘና ፈተናዎች ይካሄዳሉ ። ትምህርቱን በአስፈላጊው ሁኔታ ላጠናቀቁ ተማሪዎችም የማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት (የምስክር ወረቀት) ይሰጣል። በኮርሱም መጨረሻ ጥሩ ውጤት ላመጡት ሽልማት ይበረከታል። መመዝገብ የምትፈልጉና ማንኛውንም አይነት ከታች ባለው አድራሻ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ። +251914946589 @Asrategabriel 4.7K views16:18