Get Mystery Box with random crypto!

በመተከል ዞን በዳንጉር ወረዳ የሚገኘው የበላያ ንጉሠ #ዳዊት ገዳም የእርዳታ ጥሪ ታሪኩን ያለወ | ቀሲስ ስንታየሁ የኔአባት

በመተከል ዞን በዳንጉር ወረዳ የሚገኘው የበላያ ንጉሠ #ዳዊት ገዳም የእርዳታ ጥሪ
ታሪኩን ያለወቀው አውቆ እንዲረዳን
Share share አድርጉልን!
=====
ስለበላያ አጭር ታሪክ

የአድያም ሰገድ ኢያሱ አባት ከንግስናው ከተሻረ በኋለ የጥንት ሀገር ወደ ምትበል በላያ ንጉስ ዳዊት ቀበሌ መጣ።
ከመጣ በኀላ በያዘው ወቅታዊ በሽታ ታሞ አረፈ። የአረፈበት ልዩ ስፍራ ደጥሆ ከሚበል ጎጥ " አባ ላምታ" ሾላ ስር በክብር ተቀበረ ፡፡
ከዚህ በኋላ ልጃቸው አድያም ሰገድ ኢያሱ ንጉስ ከሆነ በኋላ አባቱ የአረፈበትን ፍላጋ መጣ ሲመጣም 7ቱን ፅላት በቄስ አባዋሬ በማስያዝ ወደ በላያ ንጉስ ዳዊት ቀበሌ መጣ ፡፡
አድያም ሰገድ ኢያሱ የአባቱ አፅም አረፎ ከተከበረው ቦታ አፅሙን ይዞ አውጥቶ ሲሄድ
እናዚህን ፅለቶችን እዚህ አባቴ ከተከበረበት ቦታ ፅላቶች ይተከሉ ብሉ ከንጉስ ዳዊት ቀበሌ አስረክቦ ሄደ፡፡
ይህ ገዳም በኢትዮጵያ ኦርተዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲን በመተከል ሀገረ ስብከት በዳንጉር ወረዳ በላያ ንጉስ ዳዊት ቀበሌ የሚገኝ ነው ።
ገዳሙ የተመሠረተውም በ1674 ዓ/ም በትልቁ አዲያም ሰገድ ኢያሱ ጊዜ ሲሆን ይህ ማለትም ቤተክርስቲያኑ 339 በላይ ዓመታት ያስቆጠረ ነው ።ይህ ገዳም ብዙ ታሪክ እና ገቢረ ተአምራት የሰራ እና እየሰራ ያለው ሲሆን

ለምሳሌ :ጠላት ፋሺስት ኢትዮጵያን በወረራት ጊዜ ከ 32 ጊዜ በአውርፕላን በተወረወረ የቦንብ ጥቃት ሳያደረስ መቅረቱን ና አውርፕላኑም ሂዶ ተረራ ለይ እንደወደቃ የወደቀበትም ቦታ እስከ አሁን ድረስ በአገውኛ "እርቡላ" ተብላ ትጣራለች፡፡ይህ ትንታዊ ገዳም የተሠራው በድንጋይና ጭቃ እንዲሁም በውስጡ የተለያዩ ጥንታዊ የብራና መፅሓፍ ያለው እና አዲስ ፋዋሽ ፀበል በቅ/ዳዊትና በቅ/ጊዮርጊስ ስም ወጥቷል።
የአሁኗ በላያ የድሮ የአውራጃው ስያሜም በለያ ነበር::
አሁን ከአውራጃ ወርዶ ምሥለኔ ወይም ቀበሌ ሆኖል:: በምትኩ ምንም ያልነበረው ዳንጉር ወረደ ሆኗል:: ይህ የሆነው በቀ/ ኃ /ሥ ዘመነ መንግስት ነበር::
በላያ ድሮ ግዛቱ በጣም ሰፊ ነበር::
በአንድ ወቅት በዘመነ መሳፍንት ግዛቱ ቋራን ፣ ደምቢያን ፣ ጉባን እና አቸፈርን ጨምሮ አንድ ላይ ነበሩ ይባላል::
የፋሲልን ግንብ የመሰሉ ግንቦች በበላያ እና በጉባ መኖራቸው የዚህ ፍንጭ ይመስለኛል::
የበላያ ድንበሩም በምሥራቅ አገው ምድር አውረጃ ዋና መናገሻዋ ደንግላ ከተማ ኪልቲ ወንዝ: በምዕራብ አሶሳ የሐጂ ሸጎሌ ሀገር እና የአሁኑ ቤንሻንጉል እና ሱዳን::በሰሜን ጎንደር፣በደቡብ መተከል አውራጃ መናገሻዋ ቻግኒ ነበር::
አፄ ኃይለ ሥላሴም በመጽሐፋቸው በላያን አውራጀ ብለው ፅፈዋል::ዋና ከተማው "ንጉሠ ዳዊት ተብሎ የሚጠራው የአሁኑ ቀበሌ ነበር ይላሉ ትላልቆቹ!
ከዛሬ 600 እና 700 ዓመታት በፊት " ዳዊት" የሚባሉ መናኝ -ንጉሥ መንነው መጥተው ገደም አድረገው አንደ መሠረቱ እና እዛው ኖረው እዛው ንጉሠ ዳዊት ቤ/ክ ውስጥ እንደ ተቀበሩም በአፋ-ታሪክ ይነገራል::
ስለ በላያ ማወቅ የሚፈልግ ሰው ከአለ" ዜና ኢትዮጵያ ከአንደኛ ፒኦሪ አስከ ላሊበላ" የሚል መጽሐፍ
በመምህር ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርዔል ገ/ኢየሱስ: የተዘከረ :
እንዲሁም " አምሰለ ገነት " የሚል በክቡር ተክለፃዲቅ መኩሪያ የተፃፉ መፅሐፍትን ማንበቡ መልካም ነው::
በተጨመሪ በንጉሥ ዳዊት የሚጠሩ ብዙ ቦታዎች አሉ::
ለምሣሌ- አዛ ዳዊት: አዛ ማለት በአካባቢው ቋንቋ በአገውኛ አዛዥ፣ንጉሥ ወይም መሪ ማለት ነው::
ጃን ወምበር( የጃንሆይ ወምበር)፣ጃን ማለትም ጃንሆይ ወይም ንጉሥ ሆይ ማለት ነው::
በአከባቢው ያሉት ከዛሬ ከ500 እና 600 በፊት የተቆረቆሩት- አብያተ ክርስቲያናት
1: ንጉሠ ዳዊት ወ ጊዮርጊስ- ገዳም ቀበሌ
2: ቅዱስ ሚካኤል- ሳንጃ ሚካኤል ቀበሌ:
3: ተክለሃይማኖት - ባርክቶች ተለሃይማኖት:
4: ቅ/ማርያም- አንከሻ ማርያም:
5: ከቅ/ጊዮርጊስ ጋር ተደርባ የነበርች ቅ/ኪዳነምህረት በኋላ እራሶን ችላ ቻምቺ ኪደነምህረት ሄዳ ተተክላላች::
6: ደቅ እስጢፋኖስ ገደም- ደንጉር:
7: ቅ/ማርያም ገደም- ዳንጉር አካባቢ:
8: ቅ/ ገብርኤል- በዳንጉር የጥንቶቹ ናቸው ::
እስከ አሁኑ ሰአት ተተክሏ እያገለገለ ይገኛል።
ይህ ቦታ በወቅቱ አንቱ የተባሉ ለጎጀም ገጂ እንዲሁም ለዣንሆይ ታማኝ አገልጋይ የነበረው የፊታውራሪ ዘለቀ ሊቁ መከና መቃብርም እዛው ከቤተክርስቲያን አጥር ስር አለ።

√በዚህ የሚነሱ አወዛጋቢ ለሆነው ነገር መልሱ ፅላቱ የአፄ ዳዊት የኢትዮጵያዊው ነው ሲሉ እንዳልሆነ ፅላቱን በዓይን ከአዩት አባቶች በተገኘ ምስክርነት ፅላቱ የእስራኤል ንጉሦ የልበ አምላክ ዳዊት መሆኑን ተረጋግጧል።
በኢትዮጵያ ደረጃ በበላያ ብቸኛው የእስራኤል ንጉሦ የልበ አምላክ ዳዊት ገዳም ነው
ቦታውን ድረስ በመሄድ በረከት እንድታገኙ በአክብሮት አሳስባለሁኝ።

ዛሬ ታሪኩን ልንገራችሁ ብቻ ሳይሆን እገዛ እንድታደርጉልን ለመጠየቅ ነው።
በአካል መሳለም መሄድ የሚፈልግ ወይም ለበለጠ ማብራሪያ 0918469330 በቴሌግራም ማውራት ትችላላችሁ ።
ስለዚህ ማገዝ በገንዘብ መርዳት የምትፈልጉ በዚህ አካውንት እንድትረዱን እያሉ እንማፀናለን።
ስም:-ንጉስ ዳዊት ገዳም ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ
በንግድ ባንክ ነው ቁጥሩ 1000446526204


ቀሲስ ስንታየሁ የኔዓባት
እንጅባራ አገው ምድር!
ሐምሌ 23/2014ዓ/ም