Get Mystery Box with random crypto!

ᴡᴏʀᴅ ᴏғ ᴛʀᴜᴛʜ®

የቴሌግራም ቻናል አርማ jesusgtruth — ᴡᴏʀᴅ ᴏғ ᴛʀᴜᴛʜ®
የቴሌግራም ቻናል አርማ jesusgtruth — ᴡᴏʀᴅ ᴏғ ᴛʀᴜᴛʜ®
የሰርጥ አድራሻ: @jesusgtruth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 449
የሰርጥ መግለጫ

"የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።"
(2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:15)
✥ ለማንኛውም ጥያቄ ወይም ምክር በዚህ ያግኙን @Adis2WOF or https://t.me/Jesuskingofkingslordoflords

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-16 14:52:44 #እንዴት_ልጸድቅ_ወይም_ልድን_እችላለሁ?

ሰው አግአብሔርን በሥራው ልያስደስተው ወይንም በእግዚአበሔር ፊት በሥራው ሊኮራና ሊጸድቅ ከቶ አይችልሞ። ምክንያቱም ከሕግ አንዱን አንኳን ሳያሟላ ሌላውን (99.9%) ሁሉ አሟልቶ ቢገኝ፣ ስለ አንዲቱ ኀጥያት በአግዚአብሔር ፊት መቆሞ ከቶ አይችልሞ፤ አግዚአብሔር ፍጹምና ጻድቅ ነውና።

#እንዴት ነው ታዲያ ሰው ከብዙ ኀጥያቱ አና ከአዳም በወረሰው የሞት ፍርድ ልያመልጥ የሚችለው? እንዴትስ መጽደቅ ይችላል? አንዴትስ ሰው አግዚአበሔርን ለያስደስት ይችላል? አንዴትስ በአግዚአበሔር ፊት መቆም ይችላል?

#መልሱ: በላከው በአንድ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ እና ብቻ ነው። “ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” ዮሐንስ 14፥6

#ምን_ልመን?

ሰው በአግዚአበሔር ፊት ብቁ ሆኖ ለመቆም በብዙ ሲሰራ እና ሲጥር፣ በሃይማኖት ድካም ውስጥም ተስፋ ሲቆርጥ ይታያል። ነገር ግን መዳንም ሆነ መጽደቅ፣ መብቃትም ሆነ ሕይወት የሚገኘው በማመን ብቻ ነው። የምናምነውም ክርስቶስ አየሱስ እርሱ የእግዚአበሔር ልጅ አንደ ሆነና ስለ ኀጢአታችን ሲል በመስቀል ላይ መሞቱ፣ መነሳቱ፣ አንዲሁሞ ወደ አባቱ ማረጉ፣ ደግሞም ዳግመኛ እንደሚመጣ ነው።

ስለዚህ “ኢየሱስ ጌታ ነው ብለህ በአፍህ ብትመሰክር፣ እግዚአብሔር ከሙታን እንዳስነሳው በልብህ ብታምን፣ ትድናለህ። የምትጸድቀውም በልብህ አምነህ ነው። የምትድነውም በአፍህ መስክረህ ነውና።'' ሮሜ 10፡9

#እኔ_እኮ_ብዙ_ሀጥያት_ሰርቻለሁ! የትኛውም የኀጠያት ጥልቀት ወይም ጥፋት ከእግዚአብሔር ፍቅር አይበልጥም። አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ይወድሃል/ይወድሻል። ከአንተ/ከአንቺ የሚጠበቀው ክርስቶስ አየሱስን ማመን ብቻ ነው። የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኀጢአት ሁሉ ያነጻናል። 1 ዮሐንስ 1:7

እግዚአብሔር እንዲሁ ይወድሃል/ይወድሻል የእግዚአብሔር ሞሕረት የትኛውንሞ ኀጢያት ያልፋል የእግዚአብሔር ጸጋ እስከ ፍጻሜ ይረዳሃል/ይረዳሻል።
161 viewsAddis A. Robele, edited  11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-04 13:10:01 "But certainly God has heard me; He has attended to the voice of my prayer. Blessed be God, Who has not turned away my prayer, Nor His mercy from me!" Psalm 66:19-20

Our Lord Jesus knows all the cares you hold in your heart, and He has heard your prayers. Rest, knowing that His heart of compassion beats for you today.

https://t.me/jesusGtruth
219 viewsAddis A. Robele, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-29 23:23:30 #የገና_በዓል_መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ነውን???
==================================
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታህሳሥ ወር አለመወለዱን ያውቃሉ???
መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል 1ቆሮ 2፡15
ዮሐንስ 8:31-32
ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፡— እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤
እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል፡ አላቸው።
1) በእውነት ኢየሱስ ክርስቶስ በታህሳስ ወር ተወልዷልን???
2) የሚደረገው ስርዓትስ ከክርስትና ጋር ግንኙነት አለው??
3) የገና ዛፉስ ከየት መጣ???
4) መብራቱ እና አፉፋውስ(ፊኛ) ከየት መጣ???
5) ቅዱስ ኒቆላዎስስ ( የገና አባት ) የተባሉት ከየት መጡ???
መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል 1ቆሮ 2:15
መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል ፦
=========================
መሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በታህሳስ እንዳልሆነ ይናገራል።
1ዜና 24፡7-19 ንጉሥ ዳዊት ካህናትን በተራቸው ወደ እግዚአብሔር መቅደስ ገብተው ያጥኑ ዘንድ መደባቸው 24 ካህናት ነበሩና በወር 2 ካህን ማለትም( ከ 1-15 እና ከ 16-30) በ 12 ወር 24 ካህናትን አደረገ ።
በእስራኤላዊያን ቀን አቆጣጠር መሰረት ደግሞ የመጀመሪያ ወራቸው ኒሳን (Nisan) ይባላል።
አስቴር 3፡7 , 8፡9
የእስራኤል የመጀመሪያ ወር ኒሳን በኢትዮጵያውያን ቀን አቆጣጠር ሚያዚያ መሆኑ ነው።
በምድቡም መሰረት
=====================
በአንደኛው ወር (ኒሳን)
ከ 1-15 ቀን== ዮአሪም
ከ 16-30 ቀን== ዮዳኤ
በሁለተኛው ወር (እያር)
ከ 1-15 ቀን==ካሪም
ከ 16-30 ቀን==ሥዖሪም
በሶስተኛው ወር (ሲቫን)
ከ 1-15 ቀን==መልክያ
ከ 16-30 ቀን==ሚያሚን
በአራተኛው ወር ( ታሙዝ)
ከ 1-15 ቀን== አቆስ
ከ 16-30 ቀን== አብያ
በሉቃስ ወንጌል 1፡5- 13 #ከአብያ ቤተሰብ የሆነ ስሙ ዘካርያስ የሚባል ሰው እናገኛለን በ 4ኛው ወር (ታሙዝ) የወሩ ሁለተኛ አጋማሽ ማለት ከ 16-30 ቀን በክፍሉ ተራ ለማጠን ወደ እግዚአብሔር መቅደስ ይገባል።
በመቅደስ ውስጥ እያጠነ መልአኩ ገብርኤል ተገልጦ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረዋል ተራውንም ጨርሶ ወደ ቤቱ ይመለሳል ከዚያም ዩሐንስ መጥምቁ ይፀነሳል።
መጥምቁ ዩሐንስ በተጸነሰ በ6ኛው ወር መልአኩ ገብራኤል በናዝሬት አውራጃ ገሊላ በሚባል አካባቢ ወደምትኖር ስሟ ማርያም ወደምትባል ድንግል ሴት ያቀናል ከመንፈስ ቅዱስ እንደምትጸንስና ኢየሱስ ክርስቶስን እንደምትወልድ ይነግራታል። ሉቃ 1:26 ኢየሱስም በ 10ኛው ወር (#ቴቬት) ይፀነሳል ቴቬት 10ኛ ወራቸው በኢትዮጵያ አቆጣጠር በጥር ወር ኢየሱስ ይፀነሳል ከጥር ጀምሮ 9 ወር ስንቆጥር መስከረም (ቴስር) መጨረሻ ጥቅምት መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ይወለዳል ።
መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ የሚናገር ከሆነ የገና በዓል እየተባለ በታህሳስ ወር የሚከበረው ከየት መጣ ??
ክርስትና ከተጀመረ ከ 313 በኃላ ቤተክርስቲያን ነፃነቷን ስታገኝ ከአህዛብን አለም የመጡትን አዳዲስ አማኞች ተከትሎ የገባ የአህዛብ በዓል ነው። ታሪክ እንደሚነግረን አህዛቦች የብርሃን አምላካችን የተወለደበት ብለው ጨለማው አለፈ የበጋው ብርሃን መጣ በማለት እሳትን እያነደዱ የለመለመ ዛፍን እየቆረጡ ያከብሩ ነበር። ይህ አህዛባዊ በዓል በቤተክርስቲያን ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ተብሎ ተቀየረ ። ቆይቶም የካቶሊክ ቅዱስ የተባሉት ኒቆላዎስ የገና አባት ተብለው በየቤተክርስቲያኑ ውስጥ ተቀባይነት ካገኙ ዘመናትን አስቆጥረዋል ።
ገላትያ 4 (Galatians)
8፤ ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ፤
9፤ አሁን ግን እግዚአብሔርን ስታውቁ ይልቅስ በእግዚአብሔር ስትታወቁ እንደ ገና ወደ ደካማ ወደሚናቅም ወደ መጀመሪያ ትምህርት እንዴት ትመለሳላችሁ? እንደ ገና ባሪያዎች ሆናችሁ ዳግመኛ ለዚያ ልትገዙ ትወዳላችሁን?
10፤ ቀንንና ወርን ዘመንንም ዓመትንም በጥንቃቄ ትጠብቃላችሁ።
11፤ ምናልባት በከንቱ ለእናንተ ደክሜአለሁ ብዬ እፈራችኋለሁ።
የገና በዓል እንዲህ ስር የሰደደ እና በብዙኀን ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም እውነት ሊሆን አይችልም እውነቱ የእግዚአብሔር ቃል የሚናገረው ብቻ ነው።
ከተወለደበት ቀን ይልቅ ወደ ተወለደው ማንነት መዞር ይሁንልን ቀኑ ሳይሆን ኢየሱስ ነው መፍትሄው
"ኢየሱስም ሞቱን እንድናስብ ነው ያዘዘን"
ይሁዳ 1፡17
እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤
የወንጌል እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ
Gospel truth ministry Jimma
https://scontent.fbjr1-1.fna.fbcdn.net/v/t39.30808-6/s640x640/270249283_4659435117505365_6194869167693240219_n.jpg?_nc_cat=100&ccb=1-5&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=SUFgz9wUb4UAX-__Zbc&_nc_ht=scontent.fbjr1-1.fna&oh=00_AT-koXMWvUrS61d1ZuCUUu1jASLyH3TksjU9BX28hUWaKA&oe=61D1E949
348 viewsAddis A. Robele, 20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-17 21:21:45 Isaiah 41:10-12
"So do not fear, for I am with you; do not be dismayed, for I am your God.

I will strengthen you and help you; I will uphold you with my righteous right hand.

All who rage against you will surely be ashamed and disgraced;

those who oppose you will be as nothing and perish. Though you search for your enemies, you will not find them.

Those who wage war against you will be as nothing at all."

https://t.me/jesusGtruth
328 viewsAddis A. Robele, 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-01 03:56:03 "Your purpose is greater than your failures and mistakes." Dr. Myles

"For I am confident of this very thing, that He who began a good work in you will perfect it until the day of Christ Jesus." #Philippians_1:6

https://t.me/jesusGtruth
290 viewsAddis A. Robele, 00:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-27 19:19:14 መዳናችንን ልናጣው እንቸላለንን??

መዳናችንን ያገኘነው በ ኢየሱስ ክርስቶስ በተደረገልን ፀጋ ነው እንጂ በራሳችን ድካም እና ጥረት አይደለም ።
.ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
ይህም ፀጋ በ ልጁ አምነን የ ዘላለም ሕይወትን እንድናገኝ ነው።
.“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
— ዮሐንስ 3፥16
ጌታ የሰጠን የዘላለም ሕይወት በ ፀጋ የተገኘ ቢሆንም ነገር ግን ፀጋው የ ኅጢአት ፈቃድ አይደለም የዳነ ሰውም በኃጥያት ሊመላለስ በጨለማ ሊኖር አይፈቀድለትም።
.ሮሜ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? አይደለም።
² ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን?
የተሰጠን ፀጋ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን እና ሀጥያተኝነትን እንድንክድ የሚያደርግ ነው።
.ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤
መዳን የሚገኘው በ ሂደት ሳይሆን ሰው ባመነበት ቅፅበት ወድያው ይድናል።
.“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
ነገር ግን ድህነት አንዴ ድኛለው ተብሎ ችላ ሚባል ነገር ሳይሆን እስከመጨረሻው ልንፈፅመው የሚገባን ነገር ነው።
.“ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤”
— ፊልጵስዩስ 2፥12

ስለዚህ ስለምንሰማው ነገር ልንጠነቀቅ ይገባል የተሰጠንን ትልቅ መዳን ልንዘነጋው አይገባንም ይህን መዳን ቸል ካልነው ከ ቁጣው ብድራት ልናመልጥ አንችልም ።
.ዕብራውያን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት እንዳንወሰድ፥ ለእርሱ አብልጠን ልንጠነቀቅ ያስፈልገናል።
² በመላእክት የተነገረው ቃል ጽኑ ከሆነ፥ መተላለፍና አለመታዘዝም ሁሉ የጽድቅን ብድራት ከተቀበለ፥ እኛስ እንዲህ ያለውን ታላቅ መዳን ቸል ብንለው፥ እንዴት እናመልጣለን?
የ እውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ከፀደቅን እና ከዳንን በኋላ ወደን እና ፈልገን ኃጢያት ብንሰራ ለ ኃጢያትአቺን ማስተሰርያ መስዋዕት አይቀርብልንም ።
የዳነ ሰው ወደ ሀጥያት ከተመለሰ
1. የ እግዚአብሔርን ልጅ እረግጧል
2. የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ እርኩስ ነገር ቆጥሯል
3. የ ፀጋውን መንፈስ አክፋፍቷል
.ዕብራውያን 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁶ የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ኃጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህነበር ኃጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፥
²⁷ የሚያስፈራ ግን የፍርድ መጠበቅ ተቃዋሚዎችንም ሊበላ ያለው የእሳት ብርታት አለ።
²⁸ የሙሴን ሕግ የናቀ ሰው ሁለት ወይም ሦስት ቢመሰክሩበት ያለ ርኅራኄ ይሞታል
²⁹ የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?)
በ ጌታ ኢየሱስ እውቀት ከ ዓለም እርኩሰት ያመለጠ እና የዳነ ሰው ከ እንደገና ወደ እርኩሰት ቢመለስ ፍርዱ ታላቅ ነውና የ ፅድቅን መንገድ ባላወቃት ይሻለው ነበር ።
2ኛ ጴጥሮስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።
²¹ አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና።
²² ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ፦ የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል።
ስለዚህ የተቀበልነውን መዳን በ ጥንቃቄ ልንይዘው ይገባል ካልሆነ ከ ክርስቶስ ኢየሱስ የተለየ ኑሮ ቁጣ እና ፍርድ ነው መጨረሻው።
ለምሳሌ ዴማስ በ ኢየሱስ አምኖ የዳነ እና ከነጳውሎስ ጋር የሚያገለግል ወንድም ነበር።
.“አብረውኝም የሚሰሩ ማርቆስና አርስጥሮኮስ ዴማስም ሉቃስም ሰላምታ ያቀርቡልሃል።”
— ፊልሞና 1፥24
ነገር ግን ይህን መዳን ቸል ብሎ አለምን ወዶ የዘላለም ሕይወቱን አጥቷል።
.“ዴማስ የአሁኑን ዓለም ወዶ ትቶኛልና፥ ወደ ተሰሎንቄም ሄዶአል፤ ቄርቂስም ወደ ገላትያ ቲቶም ወደ ድልማጥያ ሄደዋል፤”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥10
እኛም ደሞ የተደረገልንን መዳን አቅልለን እንዳናየው ለራሳቺን እንጠንቀቅ ፃድቅ በ እምነት ይኖራል እንጂ እምነቱን ለመጣል ወደ ኋላ አያፈገፍግም።
.ዕብራውያን 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁸ ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።
³⁹ እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም።
የ ኃጢያት ደሞዝ ሞት ነውና በ ሀጥያት ፀንተው የሚኖሩም የዘላለም ሕይወት የላቸውም።
.ገላትያ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥
²⁰ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥
²¹ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም
የ ክርስቶስ ኢየሱስ ነኝ የሚል የ ስጋን ምኞት አይፈፅምም።
.“የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።”
— ገላትያ 5፥24
ፀጋ ከናንተ ጋር ይሁን
በ ወንደም ዴቭ
@jesusGtruth
2.7K viewsDave Rbr ሮሜ 10:9, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-27 09:19:07 ኢየሱስ አማላጅ ነው!!!

" የ ኢየሱስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ "

"ክፍል አንድ"

ምልጃ ማለት በሁለት አካላት መካከል ባለ ጠላትነት ወይም በተፈጠረ አለመስማማት በሌላ ሶስተኛ ወገን የሚቀርብ ፀሎት ፣ልመና እና የማስታረቅ ክንውን ነው።
ምልጃ በ በዳይ እና በ ተበዳይ አካላት የተፈጠረን ግጭት ለመፍታት ሌላ ሶስተኛው ወገን በ በዳዩ ስም ተበዳዩን የሚለምነው ልመና ነው።
አማላጅ ማለት ደግሞ በሁለት የተጣሉ፣ የተራራቁ፣ የተቀያየሙ አካላት መካከል ገብቶ እርቅን ለማምጣት ወይም ለማስታረቅ ምልጃን የሚያቀርብ ነው።
ኢየሱስ አማላጅ ነው ወይም ያማልዳል ሲባል በ ሰው እና በ እግዚአብሔር መካከል የነበረውን ጠላትነት ለመሻር ፣የሰውን ልጅ ከ እግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ፀሎትን ፣ ልመናን እና ምልጃን የራሱን ደም በማፍሰስ አቅርቦለናል ማለት ነው ።
የ ኢየሱስ ክርስቶስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ከ ብሉይ ኪዳን ጀምረን እስከ አዲስ ኪዳን ያሉትን ከዚህ በታች እንመልከት:-

1). “ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”
  — ኢሳይያስ 53፥12
ነብዩ ኢሳያስ ከ ኢየሱስ ልደት ሰባት መቶ ዓመት አስቀድሞ ስለ ኢየሱስ ምልጃ ተናግሯል።
ኢሳያስ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ ማለቱ ሃጥያተኞች ሳለን አመፃችንን እንዳይቆጥርብን ወደ እግዚአብሔር ለመነልን ።( ሉቃ 23:34)
" ማለደ " የሚለው ቃል የ ዕብራይስጥ አቻው (יַפְגִּֽיעַ׃) ወይም (yap̄-gî-a‘) የሚል ነው ትርጉሙም አማለደ ማለት ነው።
የ እንግሊዘኛ አቻውም ( made intercession ) የሚል ነው ትርጉሙ ምልጃን አደረገ ማለት ነው።
2).
ኢሳይያስ 59
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ እውነትም ታጥቶአል፥ ከክፋትም የራቀ ሰው ለብዝበዛ ሆኖአል። እግዚአብሔርም አየ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ።
¹⁶ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው።
.እግዚአብሔር አምላክ ወደርሱ ምልጃን ሊያቀርብ የሚችል ማንም ሰው እንደሌለ በተረዳ ጊዜ የገዛ ክንዱ (ኢየሱስ ) መድሃኒት አመጣለት አማላጅም ራሱ ልጁ ሆነለት።

3 ).“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።”
  — ዮሐንስ 1፥29
ዮሐንስ ኢየሱስን የ እግዚአብሔር በግ ያለበት ምክንያት በ ሙሴ ሕግ ለ ሀጥያት ስርየት የሚሆነው ከ መንጋው በጎች በደል የሌለበት በግ ስለሆነ ነው
ዘሌዋውያን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ማናቸውም ሰው ኃጢአት ቢሠራ፥ እግዚአብሔርም፦ አትሥሩ ካላቸው ትእዛዛት አንዲቱን ቢተላለፍ፥ ባያውቅም፥ ያ ሰው በደለኛ ነው፥ ኃጢአቱንም ይሸከማል።
¹⁸ ነውር የሌለበትን አውራ በግ ከመንጋው ለበደል መሥዋዕት እንደ ግምጋሜህ መጠን ወደ ካህኑ ያመጣዋል ካህኑም ሳያውቅ ስለ ሳተው ስሕተት ያስተሰርይለታል፥ እርሱም ይቅር ይባላል።
¹⁹ እርሱም የበደል መሥዋዕት ነው፤ በእውነት በእግዚአብሔር ፊት በደለኛ ነው።
ስለዚህ ኢየሱስ ለ ምልጃ የሚቀርብ የ አዲስ ኪዳን በግ ነው ስለታረደም አማለደን።

4).ሉቃስ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
³² እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
.ጌታ ራሱ ስለ አንተ አማለድኩ ብሎ እንዳማለደ በራሱ አፍ ተናግሯል።
."አማለድሁ" የሚለው የ ግሪክ ተመሳሳይ ፍቹ "ἐδεήθην" ወይም " edeēthēn"(ኤዴቴን ) የሚል ሲሆን ቀጥተኛ ፍቺው "መለመን "የሚል ነው።
5).ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው?
³⁴ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።
. እዚህ ላይ ጳውሎስ ራሱ" ስለኛ የሚማልደው "ብሎ ኢየሱስ እንደሚያማልድ እና በ ምልጃዉም ጳውሎስ ራሱ ተጠቃሚ እንደሆነ ነግሮናል ።
."የሚማልደው" የሚለው ቃል አገላለፁ አንድ ጊዜ ብቻ ተደርጎ ስለምያበቃ ምልጃ ሳይሆን ቀጣይነት ስለሚኖረው ምልጃ መሆኑን ያሳያል ።
. "የሚማልደው " የሚለው ቃል የ ግሪኩ ተመሳሳይ ቃሉ " ἐντυγχάνει" (ኢንቱግካኖ)
የሚል ነው ትርጉሙም የሚያማለድ ወይም አማላጅ ማለት ነው ።
. እንግሊዘኛውም " interceding" ይላል አማላጅ ማለት ነው ።
የ ግዕዙ ቃል ደግሞ "ወይትዋቀስ በ እንቲአነ " ይላል ትርጉሙም ስለኛ ይከራከራል የሚል ነው ይህም ምልጃውን የሚያሳይ ነው።
6).
ዕብራውያን 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤
²⁴ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤
²⁵ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።
. ጳውሎስ በሚገርም ሁኔታ የ ኢየሱስን ምልጃ ሲያስረዳ ምልጃው ያለፈ እና ከዚህ በኃላ የማይሰራ አድርገን እንዳናስበው ሲል "ሊያማልድ" ብሎ ነው ቀጣይነቱን የገለፀው።
. እዚህ ላይም "ሊያማልድ " ለሚለው ቃል በ ግሪኩ " ἐντυγχάνειν " ( ኢንቱግካኖ ) የሚል ነው ( to intercede ) ይህም ምልጃውን ሚናገር ቃል ነው ።
. እዚሁ ቃል ላይ ማወቅ ያለብን ነገር የ ኢየሱስ ምልጃ ከ ብሉይ ኪዳን ካህናት የተለየ መሆኑን ነው የሚለየውም የነሱ ምልጃ የሚለወጥ እና በ ሞት የሚቋረጥ ሲሆን የ ኢየሱስ ግን ማይለወጥ እና ዘላለማዊ ነው ( ዕብ 7: 23-24)
. እዚህ ላይ " ሊያማልድ " ለሚለው ቃል ግዕዙ " ተንበለ " ይለዋል ይህም ምልጃውን ሚናገር ነው።
7).
1ኛ ጢሞቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
⁶ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤
. መካከለኛው ማለቱ ኢየሱስ ሰውን እና እግዚአብሔርን ለማስታረቅ በመካከል የገባ ስለሆነ ነው ።
. ኢየሱስ የ አዲስ ኪዳን መካከለኛ ያስባለው ምክኒያት ለሰው ልጆች በደል እና ሀጥያት ሲል ያፈሰሰው ደም የሚናገር፣ የሚጮህ እና የሚለምን ስለሆነ ነው ። “የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።”
— ዕብራውያን 12፥24

ይቀጥላል......
በ ወንድም ዴቭ
@jesusGtruth
Please share and follow
ጥያቄ ካለዎት https://t.me/Jesuskingofkingslordoflords
338 viewsAddis A. Robele, 06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-24 20:19:17
1.2K viewsAddis A. Robele, 17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-24 20:17:29
1.2K viewsAddis A. Robele, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-24 20:17:22
1.1K viewsAddis A. Robele, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ