ሶልያና የተሰኘ ሥራው ከግጥሙም ጭምር ፍቅር ያስያዘኝ ግጥም ነው። ስሜቱን በግልጽ ሚከተብ ገጣሚ ነው። ሥራዎቹ በፍቅር የተጎዳ ማንነት ያለው ፣ ትዝታ የለበለበው ፣ ፍቅር ማጣት የእግር እሳት የሆነበት የግልጽነት ስሜት ያለባቸው ናቸው። እኛኝ ሚመስሉ ናቸው። ብሶት አላቸው ፣ ህይወት አላቸው ፣ እውነት አላቸው ፣ ፍልስፍና አላቸው። ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር ብሎ ትዝታን ያስታምማል። ውሸት ነው ብሎ ለምናብ የሚተው ሀሳብ ይዘይራል። በድምጽ ቀድቶ ያደረሰን ግጥሙ መመሸግያ ነው። ቆሌዬ ይወደዋል። ደግሞ አገኘሁት ፣ ጠየቅኩት ፣ አመሰገንሁት። አስበኸው ሳይሆን ሆነኸው ምታገኘው ደስታ አለ አይደል ? ...እንዲያ ነው የተሰማኝ። @henokpk @henokabayneh 2.8K viewsedited 17:41