Get Mystery Box with random crypto!

Harvest Minstry

የቴሌግራም ቻናል አርማ harvestministry — Harvest Minstry H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harvestministry — Harvest Minstry
የሰርጥ አድራሻ: @harvestministry
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 142

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-16 10:27:38
15 views07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 08:30:57 “ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥57
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንኳን ለ2015 ዓ.ም የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣዔ መታሰቢያ በዓል በሰላምና በጤና ከነመላው ቤተሰባችሁን አደረሳችሁ !!

በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያገኘነው የትንሣኤው ኃይል በዚህ የእንግድነት ዘመን ድል በመንሳት በነገር ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል በመታዘዝ እና በመኖር የትንሣኤው ምስክሮች ያደረገንን ታላቅ ጸጋ አስገኝቶልናል ።

ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን !!

የመከሩ ስራ አገልግሎት ሁላችንም ባለንበት አጥቢያ በመትጋት ከጌታ የተቀበልነውን ጸጋ በመግለጥ እንድንበረታ የሚያግዝ ፣ በተጨማሪም ወንጌልን ላልሰሙ ወገኖች በማሰማት ፣ ሁላችን የጌታ ደቀመዝሙር ሆነን ጌታ አምላካችን የሚደሰትበትን ሕይወት እንደቃሉ እንድንኖር የሚያግዝ የአገልግሎት ክፍል ነው ።
ባለፉት ዓመታቶች በጌታ ጸጋ በአገልግሎቱ ውስጥ በተለያዩ መንገዶች በመተባበር አብራችሁ በጸሎት ከጎናችን የቆማችሁ ፣ ያበረታታችሁን ፤ አብረን የእግዚአብሔር መንግስት ስራ በመደገፍ ለክርስቶስ አካል በጽድቅ መታነፅ በተሰጠን ጸጋ እንድንተጋ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ የኢየሱስ ክርስቶስ የክብሩ ወንጌል እንዲታወጅ የተባበራችሁ ሁሉ ጌታ አምላክ ይባርካችሁ ! ለበረከት ሁኑ ።

በቀሪው የአገልግሎት ዘመናችን በነገር ሁሉ የጌታ አምላካችንን ፈቃድህ በመፈጸም ፣ እርስ - በእርስ በመተናነፅ በፍቅር በአንድነት ሆነን ሁላችንም በተሰጠን ጸጋ አንዱን የእግዚአብሔር መንግስት ስራ ባለንበት ስፍራ በትጋት እንድንፈፅም የአገልግሎት ክፍሉ ይመኝላችኃል ።

የአገልግሎቱ ዋና አስተባባሪ
ወ.ዊ ታምራት ቦጋለ

" ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፦ አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።”
ራእይ 1፥8
t.me/harvestministry
10 views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 07:42:24
13 views04:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 04:37:09 " ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና ፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ ።
መጨረሻቸው ጥፋት ነው ፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው ፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው ፥ አሳባቸው
ምድራዊ ነው ። " ፊሊ 3 :

በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሞት ዋና ዓላማ አምላክ እኛን ሊያስደንቀን ሁሉን ማድረግ መቻሉን ሊያሳየን ሳይሆን በአዳም ውድቀት ያጣነውን የከበረውን የዘላለም ሕይወት ሊሰጠን በዚህም ምድር ከእርሱ ጋር በመሆን ኃጢያትን እየተፀየፍን የመስቀሉን ድል እንድናውጅ ነው !!
ዛሬ - ዛሬ ብዙዎች የሃይማኖት መልክ ይዘው ነገር ግን በቃል እና በተግባር መጽሐፍ ቅዱስ መሰረት የሌለው እውነት ላይ በመመስረት ለዚህ ዓለም ገዢ የስይጣን ሃሳብ በማደር ለሆዳቸው ብለው በድፍረት የእግዚአብሔር ቃል የሚሸቃቅጡትን በቃ ! ልንላቸው ይገባል ።

አባቶቻችን ወንጌሉን ሳይበርዙ ለእውነት ቆመው ፤ ኢየሱስ ክርስቶስን አንክድም ብለው በታላቅ መከራ ያለፉትን የእምነት ጀግኖች መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረን ምሳሌያቸውን በመከተል ለእውነት እንድንኖር ነው ።

" ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤

ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤

በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤

ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።

እነዚህም ሁሉ በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳች የሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና ። "
ዕብ 11 : 35 - 40

የኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሞት ዋና ዓላማ ገብቶን እንድንኖርበት እና በእውነት ሳናፍር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንድንመሰክር እግዚአብሔር በፀጋው ይርዳን !!
መልዕክቱን ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ እናካፍል /ሼር / እናድርግ በኢየሱስ ክርስቶስ አይታፈርም ።
12 views01:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 22:01:03
20 views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 04:32:50 በዓለም እየኖርን ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሁሉ የመጣው መከራ በአንድም - በሌላ እያገኘን እኔ ከዓለም አይደለሁም በማለት እውነታን መካድ አይገባም ። “ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም።”
— ዮሐንስ 17፥15

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ የሰው ልጆችን ሁሉ ለማዳን ነፍሱን ሲሰጥ በዚህ ዓለም ስርዓት ቢያልፍም ከዓለም ክፉ ሃሳብና የጥፋት ወጥመድ ሳይደባለቅ ለእኛም የማለደው በዓለም እየኖርን እንድንጠበቅና ዓለምን የምናሸንፍበት ጸጋ እንዲበዛልን ነው ።

ከእግዚአብሔር የተወለደ ዓለምን እንደሚያሸንፍ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ፤ ከእግዚአብሔር ለመወለድ የመጀመሪያው ተቀዳሚ ተግባር የሰው ድርሻ ኃጢያተኛ መሆኑን አምኖ በራሱ መንገድና የፅድቅ ስራ እንደማይድን ተገንዝቦ ፈጣሪ አምላክ ለሰው ልጆች / ለዓለሙ ሁሉ / በገለጠው መድሃኒት እውነት ፣ ሕይወትና መንገድ በሆነው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን ነው ።

" ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።
ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው? "
1ኛ ዮሐንስ 5 :4 - 5

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ክፋትና ተንኮል በመግለጥ ሰዎች ከወጥመዷ እንዲያመልጡ በማስተማር በፍቅር አሸንፎአል ።

ወድ ወገኖች እኛ እየኖርንባት ስላለችው ዓለም ያለን እውቀት ምን ይመስላል ? ዛሬ ላይ ዓለም አንድ መንደር በሆነችበት ጊዜ ሌላው አህጉር የተከሰተው ችግር የሁሉ እየሆነ በጤና ፣ በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ ሕይወት እንቅስቃሴያችን አሉታዊ ተጽእኖ በማሳረፍ በብዙ እየጎዳን ይገኛል ።

አንዳንዶቻችን ተስፋ በመቁረጥ ይህች ጠፊ ዓለም ነች ስለዚህ ዝም ብሎ መኖር ነው በማለት ይባስ ለክፉ የዲያቢሎስ ሃሳብ ተጋልጠው በተሸናፊነት የሚኖሩት ቁጥር ቀላል አይደለም ። እውነቱ ግን ይህ አስተሳሰብ ከመጽሐፍ ቅዱስ መሰረታዊ አስተምሮ ጋር የሚቃረን ነው ።

እግዚአብሔር ይህችን ዓለም ፈጽሞ ለተወሰነ ስዓት ቢተዋት የሚውጠውን ፈልጎ ዙሪያችንን እንደሚያገሳ አንበሳ ዙሪያችንን የሚዞረው ዲያቢሎስን 1ኛ ጴጥ 5 : 8 እንደተገለፀው ሁላችንንም ባጠፋን ነበር ።
እግዚአብሔር ለአንድ ደቂቃ ዓለምና በውስጧ ያለነውን ሕዝብ ፈፅሞ አልጣልም መሰረታዊው እውነት ግን በዓለም ሳለን በመከራ ማለፋችን ግድ ነው ምክኒያቱም የምንኖረው በኃጢያት በወደቀ ዓለም እንደመሆኑ እያንዳንዳችን በግልና በጋራ የምናልፍባቸው አሰቸጋሪ የፈተና ወቅቶች በሕይወታችን ዘመን ይገጥመናል።

በአሁኑ ወቅት ዓለማችን እስከዛሬ ካጋጠሟት በከፋ ሁኔኘታ የኮሮና ቨይረስ በተጓዳኝ ይዞት የሚመጣቸው ችግሮች የከፋ መሆኑን የኢኮኖሚ ተንታኞች በስፋት እየነገሩን ይገኛሉ መጽሐፍ ቅዱስም የመከራው ማብቂያ እስከ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ድረስ እየጨመረ ይመጣል እንጂ ፈጽሞ ይጠፋል ብሎ አይነግረንም ። ማቴ 24

የመጨረሻው ዘመን የሚያስጨንቅ 2ኛ ጢሞ 3 : 1 - 5 እንደመሆኑ መጠን የሰዎች ፈርሃ እግዚአብሔር የሌለበት መጥፎ ባህሪ ክሰይጣን ሸንገላና ማታለል ጋር ተደምሮ የዚህችን ዓለም መከራ በይበልጥ አባብሶት ይገኛል ።

በመከራ ወስጥ ለሚያልፈው የሰው ልጅ ማብቂያ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር ያዘጋጀለትን የከበረ ተስፋ በዚህ ምድር በእምነት ጨብጦ ከዓለም ክፋትና ወጥመድ በማምለጥ በጎ ተጽእኖ እንዲያመጣ ለምድር እንደ ብርሃንና ጨው ጠቃሚ አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ።

ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና አገልግሎት የምንማረው በተሰጠን ዘመን በዋናነት ለትውልዱ የሕይወትን ቃል በማቅረብ በበጎ ጠቃሚ ስራ የተሰጠንን ኃላፊነት መወጣት ነው ።

" ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።
በዓለም ሳለሁ የዓለም ብርሃን ነኝ ። "
ዮሐ 9 : 4 - 5
በዓለም ውስጥ የመኖሩ ዓላማ የጠፋበት የሰው ልጅ ትክክለኛ ሰው ሆኖ ለተፈጠረለት የከበረ ሕይወት ገብቶት መኖር የሚችለውና ከዘላለም ኩነኔና ፍርድ የሚያመልጠው ፤ አምላክ ከክብሩ ወርዶ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተጸንሶ በማርያም ማህፀን በማደር የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ በተገለጠው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያምን ነው ።
ሉቃ 1 : 26 - 38

መጽሐፍ ቅዱስ ለሰዎች አንድ ጊዜ መሞት ከዚህ በኃላ ፍርድ እንደተመደበባቸው ይነግረናል ፤ በመጀመሪያው ሞት ሁሉም የሰው ልጅ ከዚህ ምድር በተለያየ ጊዜ በመጠራት ማለፉ ግድ ነው በርካቶች ወዳጆቻችንም ሆኑ ዘመድ ቤተሰቦች አልፈዋል ነገር ግን ትልቁ የሞት - ሞት በእግዚአብሔር ለሰው ልጆች ድነት የተሰጠንን መድሃኒት አቅለን ፣ የተፈጠርንበትን ዓላማ ስተን በምድራዊ ሕይወታችን እራሳችንን ሸንግለን በከንቱ ካለፍን ብቻ ነው ።

" በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ።
ዓለምን ላድን እንጂ በዓለም ልፈርድ አልመጣሁምና ቃሌን ሰምቶ የማይጠብቀው ቢኖር የምፈርድበት እኔ አይደለሁም ።
የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው ፤ እኔ የተናገርሁት ቃል እርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል። "

ዮሐ 12 : 46 - 48

በዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ በመዳን የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እየተመራ ለሰው ልጆች ድነት እየማለደ በመፀለይ የምስራቹን የወንጌል ቃል በቃልና በኑሮ በመመስከር ከእግዚአብሔር የተቀበለውን የጸጋ ስጦታና የተፈጥሮ ችሎታ በባለአደራት ትውልድን በመጥቀም በተሰማራበት መስክ እንዲያገለግል ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተገለጠው የእግዚአብሔር አምላክ ፈቃድ ነው ።

የእኛ ሕይወትና ኑሮ ምን ይመስላል ?


“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
2ኛ ቆሮ 13፥14

የጸሎት ጥሪ በዓለማችን ለገጠመን ዘርፋ ብዙ ችግሮች በእግዚአብሔር ፊት ለሰው ልጆች ድነት የተለያዩ የጸሎት ርዕሶች በመለዋወጥ የሚፀለይበትን የቴሌግራም ቻናል በጸሎት ለመቀላቀል እንዲሁም የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን ለማግኘት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጠቀም በጋራ ማገልገል ይቻላል ።

t.m/harvestministry
24 views01:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 03:33:50 ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ሆሣዕና በማለት ሕዝቡ እየዘመሩ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ ተቀበሉት ፤ ሆሣዕና ማለት አሁን አድን የሚል ትርጓሜ ይሰጠናል ።

በትንቢት ተነግሮ በመጽሐፍ ቅዱስ የተፃፈው መልዕክት እንዲሁ ፍፃሜውን ያገኘበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ሁሉ ለማዳን ፈቅዶና ወስኖ እራሱን በመስጠት ፍቅሩን የገለፀበት በምላሹም ሕዝቡ በደስታ ዝማሬ ፦

" የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም ፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር ። "
ማቴ 21: 6 - 11
ይህ ታላቅ የምስጋና ዝማሬና የነፍስ ጩኽት ናፍቆቱ የእግዚአብሔርን ማዳን ትድግና ነው ።

በትንቢት መዝሙር (118) : 25 - 27

" እግዚአብሔር ሆይ እባክህ አድነን ፤ እግዚአብሔር ሆይ እባክህ አሳካልን ። በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ብሩክ ነው ። ከእግዚአብሔር ቤት ባረክናችሁ ። እግዚአብሔር አምላክ ነው ብርሃኑንም በላያችን አበራ ፤ .. "
ይላል ።
ይህ ታላቅ የእግዚአብሔር የማዳን እቅድ ንጉሱ ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም የሚጠብቀውን መከራና ሞት እያወቀ የዘልዓለም ሕይወት ለእኛ ለማስገኘት ከኃጢያትና ከሰይጣን ባርነት ነፃ ሊያወጣን አምላክ ደሙን አፍሶ አሁን አድነን የሚለውን የሕዝቡ ጥያቄ መልስ ያሰገኘበት እለት የተዘመረው ሆሣዓና የሚለው ዝማሬ ይህን እውነት ያስታውሰናል ።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት በፊት የፈፀመው ዘላለማዊ የደህንነት መንገድን አውቀውና ወስነው እርሱን ለመከተል ቃል ገብተው ነፍሳቸውን በአዳኙ ጌታ ላይ አሳርፈው የሚኖሩ እንዳሉ ሁሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተበት ዋና ዓላማ ያልገባቸው ባሉባት ዓለም ውስጥ እንገኛለን ።
የጌታን ዘልዓለማዊ ፍቅር የቀመስን የእግዚአብሔር ልጅነትን በዮሐንስ ወንጌል 1 : 12 መሰረት ያገኘን ለሌሎች ወገኖቻችን እየጸለይን ወደ መጽሐፍ ቅዱስ እውነት ተመልሰው የእግዚአብሔርን ቃል እንዲያነቡና እንዲታዘዙ እንርዳቸው ።
የእግዚአብሔር አምላካችን የልቡ ፈቃድ ምን እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ሲነግረን ፦

" ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው ።
አንድ እግዚአብሔር አለና ፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ፤
ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ ፤ "
1ኛ ጢሞ 2 : 3 - 6
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ተወልዶ አምላክ እራሱን ዝቅ ያረገበት በታላቅ መከራና ህማም የሁላችንንም በደልና ኃጢያት ተሸክሞ ያለፈበትን ዋና ሚስጥር ሁላችንም ይህንን እውነትን በማወቅና በእውነት በመኖር ፈጣሪ አምላክን ደስ ልናሰኘው ይገባል ።

እግዚአብሔር ለሁላችንም ጸጋውን ይብዛልን ።

አሜን !!!!
t.me/harvestministry
17 views00:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 05:00:06
" ቆይቼ እግዚአብሔር ደጅ ጠናሁት፥ እርሱም ዘንበል አለልኝ ጩኽቴንም ሰማኝ።
... ከጥፋት ጕድጓድ ከረግረግም ጭቃ አወጣኝ፥ እግሮቼንም በድንጋይ ላይ አቆማቸው፥ አረማመዴንም አጸና።
አዲስ ዝማሬን ለአምላካችን ምስጋና በአፌ ጨመረ፤ ብዙዎች ያያሉ ይፈሩማል፥ በእግዚአብሔርም ይታመናሉ ። "
መዝ (40) : 1 - 3
45 views02:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 03:19:56

15 views00:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 05:20:30
16 views02:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ