2022-08-06 14:39:34
♡አላህን ጠብቅ፤ ይጠብቀሃል፤ አላህን አስታውስ ይስታውስህል ዓብደላህ ኢብን ዓባስ እንዲህ አለ፡ “የሆነ ቀን ከነብዩ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ኋላ ነበርኩ። ከዛም እሳቸው አንተ ልጅ ሆይ እኔ ንግግሮችን አስተምርሃለሁ አሉኝ።
አላህን ጠብቀው (አስታውሰው) ይጠብቅሃል። አላህን ጠብቀው (አስታውሰው) ፊት ለፊትህ ታገኘዋለህ። ከጠየቅክ (መጠየቅ ከፈለግክ) አላህን ጠይቅ። ከታገዝክ (አገዛን ከፈለግክ) በአላህ ታገዝ። ህዝቦች ሁሉ
አንተን ለመጥቀም ቢሰበሰቡ አላህ ካልጻፈው በቀር አይጠቅሙህም። ህዝቦች ሁሉ አንተን ለመጉዳት ቢሰበሰቡ አላህ ካልጻፈው በቀር አይጎዱህም። መጻፊያውም ተነስቷል። መጽሃፉም ደርቋል።”
ሓዲሱን ቲርሚዚይ ዘግበውታል።
ከቲርሚዚይ ውጭ በሆኑ ሌሎች ዘገባዎች ደግሞ : “አላህን ጠብቀው (አስታውሰው) ፊት ለፊትህ ታገኘዋለህ። በምቾት ግዜ አላህን ተዋወቀው በችግር ግዜ ያውቀሃል። ደግሞ እወቅ! የሳተህ ነገር ሊያገኝህ አልነበረም፥ ያገኘህ ነገር ደግሞ ሊስትህ አልነበረም። አሁንም እወቅ! ድል ከትዕግስት ጋር ነው፣ መገላገል ደግሞ ከችግር ጋር ነው፣ ከክብደት ቡሃላ ደግሞ ቅለት አለ።”
ሰው ሁሉ ተሳሳች ነው
‹‹ረሱል ﷺ እንዲህ ብለዋል ፦ " ባትወነጅሉ ኖሮ እናንተን አጥፍቶ፣ እያጠፉ የአላህን ምህረት እየጠየቁ የሚምራቸው ሕዝቦች ይፈጥር ነበር"›› ሙስሊም ዘግበውታል
»ሰው ሁሉ ተሳሳች ነው ፣ስህተት ተፈጥሯዊ ተግባሩ ነው፣ ከነርሱ በላጩ ደግሞ ተመላሾች ናቸው።
‹‹ረሱል ﷺ እንዲህ ብለዋል ፦ "የአደም ልጅ ሁሉ ተሳሳች ነው ከተሳሳቾች ሁሉ የበለጠ ደግሞ ንስሃ ገቢዎች ናቸው"›› ቲርሚዚይ ዘግበውታል
»አንተ ስታምፀው እርሱ ሊምርህ ጸጸትህን በናፍቆት ይጠብቃል! አንተስ ምህረቱን አልናፈክምን?
««አላህም ቃል ገባ ፦
""ባሪያዎቼ ሆይ! በየእለቱ በቀንና በሌሊት ወንጀል ትፈፅማላችሁ እኔ ሁሉንም ወንጀል እምራለሁ ። እናም ወንጀላችንን ማረን በሉኝ እምራችኃለሁ።""
رَبَّنَا فَاغْفِرْ لَنَا ذُنُوبَنَا وَكَفِّرْ عَنَّا سَيِّئَاتِنَا وَتَوَفَّنَا مَعَ الْأَبْرَارِ
«ጌታችን ሆይ! ኃጢአቶቻችንንም ለኛ ማር፡፡ ክፉ ሥራዎቻችንንም ከኛ አብስ፡፡ ከንጹሖቹም ሰዎች ጋር ግደለን፤» (አሊ-ዒምራን :193)
807 viewsibro smile , 11:39