ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ | 26ኛ ሳምንት
ሀዲያ ሆሳዕና ሀሙስ ፣ ሰኔ 9 ከጠዋቱ 4 ሰዕት ከጅማ አባጅፋር ጋር የ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታውን ያካሂዳል
በሰኔ 8 ከተከናወኑ ጨዋታዎች በኋላ በ 33 ነጥቦች ስምንተኛ ደረጃ ለይ የተቀመጠው አምባሳደራችን ሀዲያ ሆሳዕና ተጨማሪ ነጥቦችን በመሰብሰብ ወደ ደረጃ ሰንጠረዡ አናት ለመጠጋት ፣ በአንጻሩ ጅማአባጅፋር ደግሞ ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት ቀሪዎቹ እያንዳንዱ የጨዋታ ሳምንታት እጅግ ወሳኝ ከመሆናቸው የተነሳ የ26ኛ ሳምንት ጅማአባጅፋር ከ ሀዲያ ሆሳዕና ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ እጅግ ተጠባቂ አድርጎታል !
ጠንካራ ፉክክር እንደሚታይበት በሚጠበቀው የ26ኛው ሳምንት የጅማአባጅፋር vs ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ ለክለባችን ሀዲያ ሆሳዕና ድል እንመኛለን
ድል ለሀዲያ ሆሳዕና