#ክርስቲያናዊ_ሥነ_ምግባር ክፍል_2 #አታምልክ ማምለክ ሲባል እምነትን ተስፋን ፍቅርን በአምላክ ላይ መጣል ነው ።1ሰው እምነቱን ተስፋውን ፍቅሩን ከእግዚአብሔር ላይ አንስቶ በሌሎች አማልክት ላይ ሲጥል ነው ሌላ አምላክ አመለከ የሚባለው ። #አምልኮት በተግባር የሚውለው በሚከተሉት ነገሮች ነው #1በስግደት #2ጸሎት #3መስዋዕት #4ውዳሴ #5መገዛት #6ፍርሃት ወዘተ ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ከእግዚአብሔር ውጪ ለሌላ ነገር ብንሰጣቸው ሌላ አመለክን ማለት ነው ። ይህን ህግ የሚያፈርሱ ሰዎች ብዙ ዓይነት በደል ይበድላሉ ። ይኸውም #1የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር የተባለውን ትዕዛዝ ይለውጣሉ #2ከቤተክርስቲያን አንድነት ውጭ ይሆናሉ #3ተስፋ ቢስ ሁሉ የጨለመባቸው ሆነው ይገኛሉ ። #ሌሎች_አማልክት_የተባሉት ፦ ሰው እንደ እግዚአብሔር የሚያያቸውና ብቸኛውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ የሚሰጣቸው ነገሮች ሁሉ አምላክ ሊሆኑበት ይችላሉ ። እነሱም ፦ #1 ገንዘብ ማቴ 6:24 #2የሰው ሃይል ኤር 17:5 #3የሰው ጥበብ እውቀት ኤር 9:23 #4ሆድ ራስ ወዳድነት #5 የምንታመንባቸው ሰዎች (ባለ ሃብት ባለ ስልጣን ) #6አባትና እናት #7ተድላ ደስታ #8የተቀረፀ ምስል ዘፀ 20:4 አምልኮ ከእግዚአብሔር ውጪ ለማንም አይሰጥም ። አክብሮትና የጸጋ ስግደት ግን ለቅዱሳን መላዕክት እና ለቅዱሳን ሁሉ ልናደርግ ይገባል መጽሐፍ ቅዱስ ቅዱሳንን #አማልክት ይላቸዋል ። ለምሳሌ ሙሴን ለፈርኦን አምላክ አድርጌሃለው በማለት እግዚአብሔር ነግሮታል ። በቤተክርስቲያናችን ቅዱሳንን እናከብራለን ይህ ከትዕዛዙ ወይም ከህጉ ጋር አይጋጭም የእግዚአብሔርን አምልኮትና አክብሮት ለቅዱሳን አንሰጥምና ።እንዲያውም ለእነርሱ የምንሰጠው ክብር እግዚአብሔርን ማክበር ስለሆነ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር እናቀርባለን Comment @finotebrhan @finotebrhan @finotebrhan @finotebrhan 373 views19:01