እንኳን ለብርሀነ መስቀለ በሰላም በጤና አደርሳቹ አደርሰን። የመስቀሉ ቃል 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18 የመስቀሉ ቃል የተሰቀለው የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው። ይህ ቃል የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ ነው እሱም እግዚአብሔር ነው። “በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” — ዮሐንስ 1፥1 ይህ የመስቀሉ ቃል የሚናገረው አለ ከተናገራቸው ጥቂቶቹን እንመልከት _በእኔ እመኑ ይላል ዮሐ.14፥1 _ህይወት እንዲሆንላችሁ እንዲበዛላችሁም መጣሁ ይላል ዮሐ.10፥10 _መንገድ እውነት ህይወትም እኔ ነኝ ይላል ዮሐ.14፥6 እኔ ብሎ መናገር የተገባው ነውና እኔ ካለ ሌላ የለም እያለ ነው። እናም ወገኖቼ ይህን ጌታ በማመን እና በራሳችን ላይ በመሾም ፈቃዳችንን ለሱ አሳልፈን በመስጠት የዘላለምን ህይወት ማግኘት እንችላለን። ይህን በማሰብ መስቀሉን ከጀርባ ሳይሆን ፊት ለፊት እየተመለከትን ለሱ ክብር እየሰጠን መታሰቢያ በአሉን ማክበር ይሁንልን ይህ ሲሆን መንፈሳዊ በአሉ ትርጉም ይኖረዋል እግዚአብሔርም ይከብራል! ክብር ለስሙ ይሁን መልካም ቀን! 0922659017 397 viewsErmiy, 04:58