Get Mystery Box with random crypto!

✥ ✥ ✥ #_የአባት_ምክር_፯ {ቤተሰብ መስለው፥ ሤራን ካነገቡ ሰዎች ተጠንቀቁ} ▬ ወገኖቼ፥ | አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ

✥ ✥ ✥
#_የአባት_ምክር_፯
{ቤተሰብ መስለው፥ ሤራን ካነገቡ ሰዎች ተጠንቀቁ}

ወገኖቼ፥ በእኛ ውስጥ እኛኑ መስለው ከዚህ ውጪ ደግሞ ለጠላት እንደ ይሁዳ አይነት ተልዕኮን አዝለው የሚንቀስቀሱ እንዳሉ እናውቃለን።

ከጌቶቻቸው የሚሰጣቸውን ተልዕኮ፣ አሉባልታ ወሬ፣ ሐሜትን፣ ውሸትን፣ ፍጭትን፥ ግጭትን የሚያስፋፉ፣ የቅን እረኞችን ስም የማጥፋት ሥራ የሚሠሩ፣ መሠረታዊ ባልሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ቤተሰቦቻችን እንዲጠመዱ፥ ክርክርን፣ ጭቅጭቅን መፍጠር፣ ከዋናው የእምነት ጉዳይ ማናጠብን የሚሠሩ አሉና ፍርዳቸውን አዝለው እየተንደረደሩ ያሉ መሆናቸውን እንድታስተውሉ እመክራችኋለሁ።

የማበጠሪያው እሳት እስከሚያነሣቸው ድረስ ነው። ከውጪ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን፣ አሉባልታዎችን ውስጥ ሆነው የሚያራግቡ፣ ቤተሰቡን እንበትናለን ብለው የዲያቢሎስን ሥምሪት የተቀበሉ እንዳሉ እናውቀዋለን።

እነሱ ይመስላቸዋል እኛ የማናውቃቸው። እንደው በጣም ይገርሙኛል! ጨለማ ውስጥ ሆነው በብርሃን ውስጥ የሚመላለሰውን ሰው አያየንም ነው እኮ የሚሉት¡ ልክ እንደ ራሳቸው የጨለማ አካሄድ ሁሉ ነገር በድብቅ የሚከናወን በእነሱ ስሌት የሚሄድ ይመስላቸዋል።

#_በጊዜው_ከነምኞታቸው_የሚጠረጉበት_ጊዜ_ሩቅ_እንደማይሆን_ላረጋግጥላችሁ_እወዳለሁ።

| ኢ◦ዓ◦ብ የዮሐንስ ወንጌል ት/ት ክፍል ፰-ሐ
| ከ፶፩ ፡ ፵፬ ጀምሮ እስከ ፶፫ ፡ ፳፫

t.me/Ewnet1Nat ◉
▮ http://t.me/AlphaOmega930 ◉