Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopiawinnet CDCR( ኢትዮጵያዊነት) 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiawinnetaa — Ethiopiawinnet CDCR( ኢትዮጵያዊነት) 🇪🇹 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiawinnetaa — Ethiopiawinnet CDCR( ኢትዮጵያዊነት) 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopiawinnetaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 431
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ድርጅት በሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ተመስርቶ ከመስከረም 05 ቀን 2013 ዓ.ም ጀመሮ በኢ.ፌ.ድ.ሪ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ባለሥልጣን በሰርተፍኬት ቁጥር 5099 የተመዘገበ ሃገር በቀል ድርጅት ነው።
መልእክት / አሰተያየትዋን በ @ethiopiawinnet1 ወይም 09 65858580 ይላኩልን።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-06 03:31:19

73 views00:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 17:36:35 ሻለቃ ዳዊት ወ/ጎዮርጊስ ላለፉት አራት ዓመታት ጎሳና ሃይማኖት በመለየት እየተደረገ ስላለውና አሁንም ተባብሶ የቀጠለውን ጭፍጨፋ በተመለከተ፤ ‘‘እያደባ በመስፋፋት ላይ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል (Creeping Genocide) በሚል አርእስት ባስነበቡት ረዘም ያለ አርቲክላቸው እንዲህ ሲሉ ትዝብታቸውን ይገልጻሉ፤

ብዙዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈፀሙትን ወንጀሎች በስማቸው ለመጥራትና የዚህ መንግሥት ፖሊሲዎችን ለማውገዝ ፈቃደኞች አይደሉም፡፡ አሜሪካውያን፣ አውሮፓውያንና መላው ዓለም ለዘር ማጥፋት ወንጀልና በሰው ልጆች ላይ ለሚፈፀሙ ወንጀሎች ሰለባዎች ያሏቸውን በጐ ስሜቶች በማሰባሰብ ንቅናቄ መፍጠር አልቻሉም፡፡ ብዙዎቹ አጥር ላይ ተንጠልጥለዋል፣ ወይም ከአጥሩ ወዲያ ማዶ የመንግሥት ካምፖች ውስጥ መሽገዋል — የያዙትን (ያላቸውን) ወይም በኢትዮጵያ ሊኖራቸው የሚፈልጉትን ላለማጣት በኢትዮጵያ ስላለው እውነታ ከመናገርና ከመፃፍ ይልቅ መሬት ላይ ስለሌለ ጉዳይ ምሁራዊ ውይይት ማድረግን ይመርጣሉ፡፡

የዘር ማጥፋት ወንጀልን ለራስ ጥቅም ሲሉ ወይም ስለ ንግግር ነፃነት ባለን የተሳሳተ ፅንሰ ሐሳብ የተነሳ የዚህኑ ያክል ጠቃሚ የሆነውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ፖለቲካዊና ሞራላዊ ገፅታዎች መካድ የወንጀሉ አባሪ ተባባሪ መሆን ነው፡፡

የዩጐዝላቪያና የሩዋንዳ ዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤቶች መተባበርን የፍርድ ቤቱ ሥልጣን በሚያዝበት ስፍራ ለተፈፀመ ወንጀል ሁሉንም ዓይነት እርዳታ ወይም ከፍተኛ መገፋፋት/ማደፋፈር ያደረገ ወይም ተፅእኖ ያሳደረ በማለት ይገልፀዋል፡፡ ይህን በተመለከተ የዩጐዝላቪያ ዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ የሚከተለውን ብሏል፡፡

“ምንም እንኳን አንዳንድ የቡድን አባሎች ብቻ በአካል የወንጀሉን ድርጊት ቢፈፅሙም … አብዛኛውን ጊዜ የወንጀሉን ድርጊት በማመቻቸት ረገድ የሌሎች የቡድኑ አባሎች አስተዋፅኦ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም የዚህ ዓይነቱ ተሳትፎ ሞራላዊ ክብደት አብዛኛውን ጊዜ የተጠቀሰውን ድርጊት ከፈፀሙት አያንስም ወይም አይለይም፡፡”

ፕሮፌሰር ሻባስ እንደሚለው፤ “መተባበር አንዳንድ ጊዜ በሁለተኛ ደረጃ ተሳታፊነት ይገለፃል፡፡ ሆኖም ወደ ዘር ማጥፋት ወንጀል ስንመጣ “ሁለተኛ ደረጃ” የሚባል ነገር የለም፡፡”
እናም ያለ ምንም መሸፋፈንና ጉንጫ አልፋ ክርክሩን ትተን በሀገራችን ኢትዮጵያ የፈጣሪ አምሳል በሆኑት በክቡሩ የሰው ልጆች ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሁላችንም ልናወግዘው ይገባናል!!

Dawit Wolde Giorgis is the Executive Director of The Africa Institute for Strategic and Security Studies
92 views14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 07:18:49
" ከሟቾች መካከል ሴቶች እና ህፃናት ይገኙበታል " - የቲክቫህ አባል

ዛሬ በቄለም ወለጋ ለምለም ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል።

እሱና ቤተሰቦቹ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባል ዛሬ የተፈፀመው ጭፍጨፋ እጅግ በጣም አሳዛኝ እንደነበር ገልፆ በርካታ ሰው ተገድላል፤ ሴቶች እና ህፃናትም ይገኙበታል ብሏል።

በአካባቢው ኔትዎርክ ይሰራ ነበር አሁን ላይ እየሰራ አይደለም ቤተሰቦቼ ቦታው ላይ ነበሩ አምልጠው ማቻራ የምትባል አካባቢ ገብተዋል ፤ ሲል ገልጿል።

ጥቃቱን እስካሁን የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አረጋግጠዋል ፤ " ጨፍጫፊዎቹ የሸኔ ቡድን " ናቸው ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " የጸጥታ አካላት ከሚያደርሱበት ዱላ የፈረጠጠው የሸኔ ቡድን በምዕራብ ወለጋ በዜጎች ላይ አደጋ እያደረሰ በመሸሽ ላይ ነው " ብለዋል።

" በኦሮሚያ ክልል፣ ቄለም ወለጋ ውስጥ የሚገኙ ዜጎች ጭፍጨፋ ተፈጽሞባቸዋል " ሲሉ ፅፈዋል።

" በዜጎቻችን ላይ በደረሰው መከራ እያዘንን ይሄንን አሸባሪ ቡድን እስከመጨረሻው ተከታትለን ከህዝባችን ጋር እናስወግደዋለን። " ሲሉም አክለዋል።

ከጥቂት ቀናት በፊት በምዕራብ ወለጋ ቶሌ ቀበሌ መንግስት በይፋ ባመነው ብቻ ከ300 በላይ ሰዎች መጨፍጨፋቸው ይታወሳል። በወቅቱ ተገድለው የተቀበሩ በአንድ አካባቢ ብቻ እስከ 600 እንደሚደርስ ቤተስቦቻቸው እዛው ያሉ የቲክቫህ አባላት መናገራቸው አይዘነጋም። አንዳድን ተቋማት ቁጥሩን ከዚህም ከፍ ያደርጉታል።

አሁንም ንፁሃን ፣ ምንም ስለፖለቲካ የማያውቁ ህፃናት፣ ሴቶች እየተገደሉ ሲሆን ከቀናት በፊት የነበረው የንፁሃን ጭፍጨፋ ሰሞነኛ አጀንዳ ሆኖ አልፎ ነበር።

በድጋሚ የመንግስት ተቀዳሚው ተግባሩ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ በመሆኑ ለንፁሃን ዜጎች ጥበቃ ሊደረግ ይገባል።

@tikvahethiopia
59 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 14:12:04 የኢትዮጵያዊነት ድርጅት የቦርድ አባል የሆኑት ዶ/ር ምስጋናው በአርትስ ቲቪ ተገኝተው ያቀረቡት ገለጻ


110 views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 20:26:48
https://twitter.com/IPSS_Addis/status/1541787161523003392?s=20
Public Lecture
671 views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 10:33:55
172 views07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 16:19:45
#በቃ
237 views13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 20:57:15
በወለጋው አስቃቂ የዜጎች ጭፍጨፋ ዙሪያ የድርጅታችን ያወጣው መግለጫ
269 views17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 11:04:00 በአዲስ ችቦ፣ በአዲስ ጮራ፣ የምታብብ እንደገና።

የዓለም ጥቁር ሕዝቦች ቤዛ፣ እናት ፀሐይ እናት ሰላም፣
ኢትዮጵያዊነት ፍቅር ናት፣ የአፍሪካ ዘለዓለም ገዳም፣
ያጠፋትን እያጠፋች፣ ታበራለች እንጂ አትጠፋም።
ኢትዮጵያ ዘለዓለም ሰላም፣ ዘላለም ፀሐይ ብሥራት፣
ለዓለም ሥልጣኔ ቁንጮ፣ ለዓለም የጥቁር ዘር ኩራት፣
ለወዳጆቿ ብርሃን፣ ለጠላቶቿ ግን እሳት፣
“እጆቿን ወደ እግዚአብሔር፣” ዛሬም “እንደ ዘረጋች” ናት።

ብሩህ እንጂ ምጡቅ ጥበብ፣ ኢትዮጵያዊነት መች በእልክ፣
የሚካኑበት ቅጥፈት ነው፣ በዘረኝነት ንትርክ?'
የኢትዮጵያዊነት ጥበቡ፣
መደናበር ሳይሆን ግቡ፣
በሆድ አምላክ ከመታወር፣
በደም ጭቃ ከመነከር፣
ለንቅዘት ጣኦት ከመስገድ፣ ተፈቃቅዶ በመከበር።

መቻቻል ነው በአገር ሕብረት፣
በአርቆ ማስተዋል ምሥጢር፣ አንድነት በካበተበት፣
ለነገው ትውልድ ተስፋ፣ አዲስ ጎህ እንዲታይበት፣
የልዕልና መክሊት ነው፣ ራዕይ ነው ኢትዮጵያዊነት።

ስማችን ዛሬ ቢበዛም፣
ማሞካሻችን ቢንዛዛም።
አንዳንዴ “በነፍጠኝነት፣” አንዳንዴም “በውሾች” ጩኸት፣
አንዳንዴም “በሃድጊ” ጭነት፣ አንዳንዴም “በጨርቅ” ዝትት፣
መንፈሳችንን ለማቁሰል፣ ያለለከት ብንጠራም፣
ኢትዮጵያዊነት ርቱዕ ነው፣ በነቀዝ አፍ አይፈታም።
ምክንያቱም ከመሠረቱ፣ በኢትዮጵያዊነት እምነቱ፣
ሕዝብን ነፃ ማውጣትና፣ ነፃነት መንጠቅ ዓይነቱ፣
የተለየ ነው ሥርዓቱ።

ለሕዝብ ነፃነት ገድል፣ ሕይወቱን መስዋዕት አርጎ፣
እንደገና ነፃነቱን ከሕዝቡ እጅ ሰንጎ፣
በጠመንጃ ጉልበት ነጥቆ፣ የዓለም ዴሞክራሲን ሸማ፣
የሃፍረት ማቅ አከናንቦ፣ የኢትዮጵያዊነቱን አርማ፣
በአንድ አናሣ ጎሣ ቡድን፣ በዘረኝነት ግፍ አድማ፣
በአደባባይ እያደማ፣ ነፃ አውጪ ነኝ ማለት ደሞ፣
ለዕብሪተኝነት ነው እንጅ፣ መቼ ለነፃነት ቆሞ?!
ኢትዮጵያዊነት ምጡቅ ነው፣ ለዕኩይ ሥንዝር አይሟላም፣
በጠባብ ክንድ አይለካም፣
የዘረኝነት መቅነት፣ ለሽንጧ ቁመት አይበቃም።

ስለዚህ ኢትዮጵያዊነት፣ አስቀድሞ ራስን አውቆ፣
የካም አበው መነሻውን፣ ማንነቱንም ጠንቅቆ፣
በአንድ እናት አገር ልጅነት፣ የሕብረት ሸማ ተላብሶ፣
በዓለም ሥልጣኔ መሥራች፣ ሳይንሳዊነት ምሰሶ፣
በሥልጣኔአችን ታሪክ፣ ከፅንፍ ፅንፍ ታድሶ፣
እያስተጋቡ በርቱዕ፣ ለነገው ትውልድ ሰንደቅ፣
“ከሕዝብ ለሕዝብ በሕዝብ፣” ዴሞክራሲን ማንፀባረቅ፣
ነውና ኢትዮጵያዊነት፣ “ጥቁር-እሳት-ፀሐይ ሰላም”
ኢትዮጵያ የካም ግንድ እናት፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ገዳም
ያጠፋትን እያጠፋች፣ ታበራለች እንጂ አትጠፋም።

ጥራቱ እንደ ምንጭ ውሀ፣ ድብብቆሽ ያልከለለው፣
ብሩህ እንደ ሜሮን ፀበል፣ ኢትዮጵያዊነት ግልፅ ነው።
ይኼ ተለጉሞ መዳህ፣ ተጭቁኖ “መረጋጋት”፣
አጎብድዶ ለአምባገነን፣ እንደ መጋጃ መነዳት፣
ኢትዮጵያዊነት አደለም፤
ይኸ ፈርጥጦ ሩቅ ሆኖ፣ ከስደት ኬላ ማላገጥ፣
ከሕዝብ ሰቆቃ ሸሽቶ፣ ኢትዮጵያን በጣር ማፋጠጥ፣
ጽዋዉን አብረው ሳይቀምሱ፣ ትውልዱን ከሞት ማጋፈጥ፣
ራስን ከሃቅ ደብቆ፣ በስደት ዋሻ ማሽቃበጥ፣
ነገ በሥልጣን ኮርቻ፣ እንደ ታቦት ለመቀመጥ፣
ቀቢፀ ተስፋን ማቁነጥነጥ፣
ኢትዮጵያዊነት አደለም፤
ይኸ በቁም ተደናብሮ፣ በመገነጣጠል ሮሮ፣
ጤና እንደሌለው አእምሮ፣ በጎሠኝነት ተሳክሮ፣
ወደ ሲኦል መሽቀዳደም፣ በዘር ጥላቻ ታውሮ፣
ኢትዮጵያዊነት አደለም፤
ይኸ በቅዠት ተናውጦ፣ ማስረከብ ሰብአዊ ክብርን፣
እንደ አጋሠሥ መኮርኮዳ፣ ያው ሳይንተራሱ ክንድን፣
ኢትዮጵያዊነት አደለም፤
ግን ያለ ውድ በግዳጅ፣ ተገፍትሮ ለባርነት
እምቢኝ ማለት ለነፃነት።

ከኢትዮጵያዊነት ዓላማ ፣ በየጎጥ ሳንዘናጋ፣
ለእኩልነት መዋደቁ፣ ፅዋን መቀበል በፀጋ፣
የመንፈስ ኩራት አብነት፣ የማይተመን በዋጋ፣
አበው በደም ያወረሱን፣ ዓፀመ ርስት ነው የዜጋ።

በጎሠኝነት ትምክህት፣ ጀርባውን ጎጡ ያልቀደደው፣
አንድነታችን ከብረት፣ እንዲጠነክር እንደ አበው፣
በኢትዮጵያዊ ማተባችን፣ እንድንተምም እንደ ንብ፣
ደማችን የኢትዮጵያ ልብ፣ ግባችን የሕዝባችን ግብ፣
አገራችን ሰንደቃችን፣ ዜጋችን የኢትዮጵያ ሕዝብ
ሲሆን ብቻ ነው ዘለዓለም፣ ኢትዮጵያዊነት እሚያብብ።
240 views08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ