የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስተር የሆኑት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐረር ከተማ የሚገኘውን የመንፈሳዊ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና የሐረር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጉብኝት አደረጉ፡፡
የጉብኝቱ አለማ የተማሪዎች ምዝገባ ያለበትን ሁኔታ እና የ2015ዓም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማሩን ስራ በተሳለጠ መልኩ ለማስኬድ በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል እየተደረገ ያለውን የዝግጅት ስራዎችን ለማየት መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት ሚኒስተሩ ገልፀዋል፡፡
https://t.me/EthiopianEducationalTelevision