Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopia Customs Commission

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiacustomscommission — Ethiopia Customs Commission E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiacustomscommission — Ethiopia Customs Commission
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopiacustomscommission
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.29K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-15 16:12:36
1.3K viewsYonas Damtew, 13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-15 16:10:07 በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባለፉት 11 ወራት ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተይዘዋል
********************************
የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ኤርፖርት የሚታየውን የገቢና የወጭ ኮንትሮባንድ ዝውውርን ለመግታት የሚያስችል ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡

በውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈሪ መኮነን ፤ የአዲስ አበባ ኤርፖርት በርካታ ዓለም ዓቀፍ መንገዶችን የሚያስተናግድ ከመሆኑ የተነሳ የኮንትሮባንድ ፍሰቱ በየጊዜው እየጨመረ እና ውስብሰብ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

ሊጠናቀቅ ቀናት በቀሩት የበጀት ዓመት 11 ወራት ብቻ 152 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር የወጭና 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የገቢ፤ በድምሩ ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የገቢና የወጭ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከል ኤሌክትሮኒክስ፣ አደንዛዥ እፆች ፣ የጦር መሳሪያ ፣ ማዕድናት ፣ የተለያዩ ሃገራት ገንዘቦች ፣ መድኃኒቶች ፣ አዝዕርትና የዝሆን ጥርስ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስዱም አቶ ተፈሪ አብራርተዋል ::

በጉምሩክ ኮሚሽን የኢንተለጀንስና ኮንትሮባንድ ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተገኔ ደረሰ በበኩላቸው፣ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን በመከላከልና በመቆጣጠር በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመው ድርጊቱን የሀገር ደህንነት ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ የተቀናጀ ስራ ይጠይቃል ብለዋል፡፡

የኮንትሮባንድ ወንጀልን መከላከል እና መቆጣጠር ለአንድ ተቋም ብቻ የሚሰጥ ሳይሆን ሁሉንም የሚመለከት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ብሎም መላው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚገባውም አስገንዝበዋል።

የኮንትሮባንድ ዝውውር በሃገር ሰላም ፣ በህዝብ ደህንነት እና በኢኮኖሚ ላይ እያደረሰ የሚገኘውን ጉዳት ለመከላከል ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንደሚገባቸውም የውይይቱ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission
1.8K viewsYonas Damtew, 13:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 11:22:09
1.6K viewsYonas Damtew, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 11:21:43 በባህር ዳር ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ8 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያዎች እና ሌሎች የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
********************************
በባህር ዳር ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በጎንደር ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ኬላ ከ8 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያዎች እና ሌሎች የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ወደ ጎንደር ከተማ ሊገቡ ሲሉ ወለቃ ኬላ ላይ ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል 86 ፍሬ ሽጉጥ ፣ የተለያዩ ሽቶዎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ይገኙበታል፡፡

የኮንትሮባንድ እቃዎቹ በክልሉ ፖሊስ እና አድማ ብተና ፖሊስ አባሎች በተደረገው ፍተሻ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ ሶስት ተጠርጣሪዎችንም በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ ብሎም የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ለጎንደር ጉምሩክ ገቢ በማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ ለክልሉ መደበኛ ፖሊስ እና አድማ ብተና ፖሊስ አባላት ምስጋናውን ያደርሳል፡፡

የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission
1.5K viewsYonas Damtew, 08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 18:58:49
1.4K viewsYonas Damtew, 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 19:26:40
980 viewsYonas Damtew, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 18:50:19
1.1K viewsYonas Damtew, 15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 18:49:53
1.1K viewsYonas Damtew, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 18:47:30
1.1K viewsYonas Damtew, 15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 18:40:50
1.1K viewsYonas Damtew, 15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ