የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ጀርመኑ ጂአይዜድ ስምምነት ተፈራሙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጀርመኑ የልማት ተቋም ጂአይዜድ (GIZ) ጋር በፌዴሬሽናችን ሥር የሚገኘው የካፍ የልህቀት ማዕከል የመጫወቻ እና ልምምድ ሜዳን ደረጃ ለማሻሻል እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሜዳ ለመሥራት የሚያስችል የ10 ሚልየን ብር ስምምነት በትናንትናው ዕለት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሠረት ጂአይዜድ በካፍ የልህቀት ማዕከል የሚገኘውን የመጫወቻ ሜዳ ደረጃውን የጠበቀ መልኩ የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚያከናውን ሲሆን አንድ ተጨማሪ አዲስ ሜዳ ደግሞ የሚገነባ ይሆናል። ከመልሶ እና አዲስ ግንባታው በተጨማሪ ለጥገና እና እንክብካቤ ሠራተኞች የሚሰጠው ስልጠናም የስምምነቱ አካል ነው። @ethiopiabuna12t @ethiopiabunasportteam 138 viewsKᴀʟᴇᴀʙ ɢʀᴀᴘʜɪᴄꜱ, edited 13:33