Get Mystery Box with random crypto!

#ምትኬ ክፍል-14 #ደራሲ_HiLA አሁን ላይ እኔም በትንሹ ተረጋግቻለሁ ቢያንስ ድካሟን እን | ኢትዮጵያዊነት የኪነ-ጥበብ ሥራዎች በትረ ጊዮን ካስት ኤጀንት

#ምትኬ

ክፍል-14

#ደራሲ_HiLA

አሁን ላይ እኔም በትንሹ ተረጋግቻለሁ ቢያንስ ድካሟን እንደቀነስኩ አስባለሁ እናቴ አለሜ ናት በስስት ስታየኝ አንዳች ስሜት ይፈጥርብኛል በተለይ ትንሽ የተጎሳቆልኩ ከመሰላትና ፊቴ ግርጥት ካለባት እንስፍስፍ ማንነቷ የተለየ ነው ሁሉም እናቶች ቃላት ባይገልፃቸውም የኔ እናት ግን ሁሉ ነገሬ ናት ሲከፋኝ አፅናኜ አማካሪዬ፤ስደሰት ፈገግታዬ ሀሴቴ፤ ሳጠፋ መምህሬ መንገድ መሪዬ ኩራዜ ገፃሼ እናቴ ለኔ እኔ ነች ሂወቴ ነች እስትንፋሴ ነች ስጦታዬም ጭምር ድካሟን ማንነቷን መመለስ ባልችልም ቢያንስ እሞክራለሁ የሷን ሀቅ ጥቂቷን መክፈል ባልችልም እጥራለሁ እናቴ አባትም እናትም ሆና ስላሳደገችኝ የእሷን ደስታ እንጂ ሀዘኗን ማየት አልሻም ፊቷ ከቶ እንዲከፋ አልፈልግም ስለናቴ ማውራት ከጀመርኩ ማቆሚያም ማብቂያም የለኝም፡፡ መቼም አሁን ከስራ መውጫ ቀደም ብዬ ስለመጣሁ ትጨነቃለች ሳታስብ ቀድሜ ካላስረዳኀት ለነገሩ እስካወራ አጠብቀኝም ቀድማኝ ነው ምታወራው የራሷን ሀሳብ ከጭንቀትና ከፍቅር አንፃር እምታወራው አይ እማ ትለያለች እኮ
"እማ እማ "
"ምትክ ምን ሆንሽብኝ በዚህ ሰአት አመመሸሽ ወይስ ምንድነው?" ይኸው እማ እንዲ ናት ለኔ ያላት ፍቅር
"ኧረ እናቴ ምንም አልሆንኩም ዛሬ ስራም አልገባሁ የሆነ ነገር ላማክርሽም ላስፈቅድሽም ነበር እንቀመጥ እማ"
"እሺ ግን ለምን ስራ አልገባሽም የትስ ነበርሽ ምትክ"
"እማ ልነግርሽ ነው አትቆጪኛ እማ ሙች መጥፎ ነገር አልተፈጠረም እውነት"
ከዛም ከመጀመርያው ጀምሬ ነገርኳት ከዛ እናቴ ፊቷ እየተቀየረ ማንበብ አቃተኝ ትስማማ ትናደድ አላቅም እኔም ግራ ገባኝ እማ አውርቼ እስክጨርስ ዝም ብላ አደመጠችኝ ልክ ስጨርስ የተወሰነ ደቂቃ ዝም ካለች በኋላ
"ልጄ አየሽ አባትሽ ስምሽን ሲያወጣ ሁሉን ማያዬ ብሎ ነው አንቺ ልጄ በመሆንሽ እጅግ ኮራለሁ አምላክ ባርኮ የሰጠኝ የመጀመሪያዬም የመጨረሻዬም ነሽ አንቺን ወደ መንገድ መርቼ መስመር ሰጥቼሻለሁ ቀራው ያንቺ ነው አንቺን ሳሳድግ አባትሽ በሚመኘው መንገድ በራስ መተማመን ያላት ጠንካራ በራሷ የምትመራ መልካምና ሰው አክባሪ ደግሞም ደፋርና ሽንፈት እማትወድ አርጌ ነው እና ልጄ ውሳኔሽን አስቢበትና እርግጠኛ ከሆንሽ አምጫት እኔ እናትሽ አላሳፍርሽም የማርያም አራስ ነች ፈጣሪ እስከፈቀደው ከኛጋር ትኖራለች "
አመሰግናለሁ እናቴ ወድሻለሁ በቃ ለብሩክ ልደውልለት እሱ ደስተኛ አልነበረም ግን እመኑኝ አታፍሩም በኔ ውሳኔ እሺ የኔ ልጅ እኔም የጀመርኩትን ልጨርስ ደግሞ ምትክ መቼ ነው እምታስተዋውቂኝ
በቅርብ እማ
ለብሩኬ ደውዬ ነገርኩት ከዛም ከምሳ በኋላ እንደሚመጣ እና አብረን እንደምንሄድ ተስማማን ለሰናይትም ምግብ እና ጁስ እንዲወስድላት ነገርኩት ተስማማን ከዛም ወደ ሻወር ገባሁ........

ክፍል 15 ይቀጥላል.....ከተመቻችሁ

#አስተያየት ካላችሁ...

@Babilove12

#joine #share

https://t.me/Ethioenku