Get Mystery Box with random crypto!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiobooks
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.34K
የሰርጥ መግለጫ

✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 41

2022-09-03 10:46:04
234 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:00:12 የጣዝማ ማር
┈┈•✦•┈┈
አብርሃም አበበ
'
ን ብ ፤
የሰራችው ማር ተቆረጠ
የተቆረጠው ተቀመጠ

ዝ ን ብ ፤
የተቆረጠውን አረከሰ
የረከሰውም ፈሰሰ

እ ና ም ፤
ለወራት የተለፋበት
ብዙ ንቦች የሞቱለት
ላትጠቀም ዝንቦ ለክፋ
የጣዝማ ማሩ ተደፋ።
════════
ኤግሜል

https://t.me/Ethiobooks
313 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:02:39

❝ከውጪ የሚመጣ ምንም ነገር የለም። ሁሉም ነገር የሚመጣው ከውስጥ(ህ) ነው።❞
ቬቪሌ ጎጋርድ


❝ዋናው ጥያቄ ሀቅ ምንድን ናት ወይም ተፈጥሮ ከየት መጣ አይደለም። ዋናውና አንገብጋቢው ጥያቄ ልኑረው ወይስ ልሙተው ነው። ሌላዎቹ ጥያቄዎች ለመኖር ከወሰንኩ የምደርስባቸው ናቸው።❞
አልበርት ካሙ


❝አንድ ሰው ስለሚደርስበት እክልና ችግር በመጨነቅ በራሱ ላይ የሚያመጣው ጉዳት፤ ችግሩ ከሚያደርስበት ጉዳት የከፋ ነው።❞
ሞንቴን


❝በብቸኝነት ከሰው ተነጥሎ (ተገልሎ) መኖር ጥሩ ነው። ግን ይህንኑ ጥሩነት የሚነግርህ አንድ ሰው ያስፈልጋል።❞
ባልዛክ


❝ለመደሰት አንድ መንገድ ብቻ ነው ያለው። ይኸውም ከእኛ ፈቃድና አቅም በላይ ስለሆኑ ነገሮች መስጋትና መጨነቅን ማቆም ነው።❞
ኤፒክቲተስ


❝ 'አንድ ቀን' የሚባለው በሽታ ህልሞችህን ወደ መቃብር ያወርዳቸዋል።❞
ቲሞቲ ፌሪስ


ጥቅሶች
@ethiobooks
386 viewsተስፋዬ መብራቱ, 05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 10:01:41 #ሽልንጌን
>>>
ጭርታና ባዶ ነፍሷን ስትዘራ እንባዋን በሸማዋ ከፊቷ ላይ ጠርጋ፣ ሀዲዱ ላይ ተራምዳ ባቡሩ ወደወረደበት አቅጣጫ ተመለከተች። ግን ሁለት እየጠበቡ ከሚገጥሙ የብረት መስመሮች በስተቀር ሌላ አልታይሽ አላት። ከዚያን ወዲህ ስለልጇ አልሰማችም። እህቷም መጥታ አታውቅም። ሦስት ዓመት አለፈ። ልጄ ሞቶም እንደሆን ጉዱን አያለሁ ብላ ከሆዷና ከልብሷ ቆጥባ ሃያ ብር እስኪሞላላት ድረስ ፓፓያውን ከሽልማት ድርጅት እየገዛች ለማትረፍ ስትጥር ነው አንዱ መንገደኛ እገዛሻለሁ ብሎ አንድ ብር ሰጥቷት መልሱን ሽልንግ ከሰጠችው በኋላ 'አልፈልግም ፓፓያሽ በስብሷል ብሬን አምጪ' ብሎ ነጥቆ ፓፓያውን መልሶ ሽልንጓን ሳይመልስ እጇን ስትዘረጋ ረግጧት ከባቡሩ ጋር የነጎደው።

ፓፓያው በእርግጥ መበስበስ ይዟል። ገዢ ከሌለው የአትክልት ነገር ይኸው ነው። ሳይሸጥላት ብዙ ጊዜ ስለቆየባት ነበር ዋናውን እንኳን ይመልስ ብላ አሚና በሃምሳ ሳንቲም የተስማማችው እንጂ ዋጋውስ አልነበረም። ምን ነካው ሰውዬውን? የለውም እንዳይባል ያለው ነው። አለበበሱ ጨዋ፣ መልኩ የዋህ፣ ቁመናው የአዋቂ የሚመስል። የስሙኒ ቅርጫት በሽልንግ ሲገዛና የሃምሳውን ሳንቲም ሙዝ በብር ገዝቶ ሲጨምር በአንድ ዓይኗ አሚና ራሷ አይታዋለች። እንደኔ ልጅ ኖሮት ለሱ ይሆናል የሚገዛው ብላ ገምታ ነው 'መልስ አለሽ ወይ?' ብሎ ሲጠይቃት ብሩን ተቀብላ አሚና ሽልንጉን የሰጠችው። ይዞብኝ ይሄዳል ብላ ጨርሳ የምትገምተው ነገር አልነበረም።

ብቻ ... ብቻ ጫጫታ ነበር፤ ጋጋታ። ከሰውዬው ዙሪያ የነበረው ትፍግፍግ፣ ግፊያ፣ የተዘረጉ እጆች ብዙ የሚያካልቡ ነገሮች ነበሩ። አንዱ ቂጢጥ እንዳለ ከኋላው አንዱ ሲገፋው በአፍጢሙ ሊደፋ ምንም አልቀረው። ጭቅጭቁ፣ ግልምጫው፣ ከአጭበርባሪ ኪስ መጠበቁ፣ ከዚያም በላይ ባቡሩ ተነሳ ብሎ ስጋቱ ከሻጩም ከገዢውም የሚወጣው ፍራንኬን፣ ሳህኔን፣ ሲኒዬን፣ መልሴን፣ ቅራቅንቦዬን... ቀልብ የሚሰልብ ነበር።

የአሚና ፓፓያ መበስበሱን ያወቀው፣ ባቡሩ ሄድኩ የሚለውን የመጨረሻ ፊሽካ ሲያሰማ ነው። «አልፈልግም። ይሄ በስብሷል።» እንቅቡን ወደሷ ገፋላት። «ኧረ የለም ጥሩ ነው ወላሂ! አልበሰበሰም።» ተናደደ። «ቅጥፈት በአሮጊት አያምርም። ፓፓዬው በስብሷል።» በግራ እጇ የያዘችውን ብር መንጭቆ ወሰደው። ባቡሩ ለአመል ተወዛወዘ።

እንቅቧን ቶሎ ራሷ ላይ አደረገችና አንድ እጇን ደረጃው ላይ እግሩ አጠገብ አድርጋ በተራ ድምፅ «ሽልንጌን!» አለችው። «የምን ሽልንግ?» ዳግመኛ ውሸት፤ መጀመሪያ የበሰበሰ ፓፓያ ልትሸጥለት፣ አሁን ደግሞ ያልተቀበለውን መልስ ልትወስድበት። በጣም ተናደደ፣ አረረ። ሊያናግራት አልቻለም። ዓይኑን እያጉረጠረጠ ጥርሱን ነክሶ ብቻ ገላመጣት።

«ኧረ ሽልንጌን!» አለች ከባቡሩ ጋር እየተራመደች። በጣም በሸቀ። ፉርጎው ላይ የነበሩት ሻጮች እየገፏት ወረዱ። «ኧረ ሽልንጌን ... ሽልንጌን!»
የባቡሩ ፍጥነት ከአሚና እስከለያየው ድረስ የነደዱ ዓይኖቹን ከፊቷ ላይ ከተጨማደደው፣ ከከሳውና ከጠወለገው የአሮጊት ፊት ላይ አልነቀለም።

ባቡሩ ከተማውን አልፎ የቤቶች ትዕይንት በተፈጥሮ የጢሻ እና የዕፅዋት ትዕይንት እየተተካ ... እየተተካ ሲሄድ፣ ያኔ እንኳ ንዴቱ አልበረደለትም። ወደ መቀመጫውም ሲመለስ እየተናደደ ነበር። "ለምን እንዲህ አደረገች? ለምን ዋሸች? ... እርሳው!" አለ ራሱን። በመስኮት እየተንደረደረ የሚያልፈውን የገጠር ትዕይንትና ሽቦውን በራሱ እያከከ የሚያልፈውን የስልክ ብረት ይመለከት ጀመር።

ግን የአሚና መልክ አልተወውም። ዓይኑ ይቦዝና ትዕይንቱ ይሟሟል። በአሚና ነገር ይተካል። "ለምን ዋሸች?" ይናደዳል። "ለምን እኔስ ያደረኩትን አደረኩ?" ድንገት ጸጸት ንዴቱን ያቀዘቀዘለት ይመስል በአዕምሮው መጣች። አሁን ሽልንግ ቢቀርበትስ? ምን ይጎዳው ኖሯል? ዋሽታ ሽልንግ ብትወስድ የራሷ ጉዳይ ነው ከጠቀማት። ግን ጠረጠረ። የሚያታልል መልክ አልነበራትም።

ማሰብ ጀመረ። 'ቅርጫቱን በሃምሳ ሳንቲም ገዛሁ። ጥሩ ... ኪሴ ውስጥ የነበሩትን ሁለት ስሙኒዎች አውጥቼ ከፈልኩ። ሙዙን በብር ገዛሁ አ..ዎ እና ምንዛሪ አልነበረኝም። ፓፓያ ስገዛ ብሬን ሰጠኋትና መልስ ስጠባበቅ ተፋረስን። ብሬን ነጠቅኩና ኪሴ ሳደርግ 'ሽልንጌን .. ሽልንጌን' ብላ ትጮኽ ጀመር። መልስ ከሰጠችኝ ኪሴ ውስጥ መኖር አለበት።'

እንደዋዛ ኮቱ ኪስ ውስጥ እጁን ሲሰድ ሁለት ስሙኒዎችን ይዞ ወጣ። ክው አለ። ደነዘዘ። ራሱን በእጆቹ ቀብሮ አቀርቅሮ ቀረ። የአሚና «ሽልንጌን ... ኧረ ሽልንጌን ... ሽልንጌን!» የሚለው ድምፅ አስተጋባበት። ከፉርጎው እኩል!!!
━━━━━━━━
የቀድሞው የ8ተኛ ክፍል
የአማርኛ መማሪያ መጽሐፍ

https://t.me/Ethiobooks
414 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:00:17 ሽ ል ን ጌ ን
══❁══
ተስፋዬ ገሰሰ
'
ባቡሩ መንቀሳቀስ ሲጀምር
«ኧረ ሽልንጌን ... ሽልንጌን» እያለች ትጮኽ ጀመር። ከባቡሩ ሞተር ግምግምታና ከተሳፋሪዎቹና ከሻጮቹ ጫጫታ በላይ ለማሰማት የሚጣጣር ኡኡታ ነበር።
«ሽልንጌን ... ኧረ ሽልንጌን!» ባቡሩ ኃይለኛ ፊሽካውን በሞተሩ 'ጃስ ጃስ' ላይ አከለበት። የተንጠላጠሉት ሻጮች ጡብ ጡብ እያሉ ወረዱ። ፍጥነቱ ሲጨምር፣ ግስገሳው ሲቀጥል በዚያው መጠን የአሚና አቤቱታ እየቀነሰ፣ ወደኋላ እየቀረ ሄደ።

ፓፓያ የያዘችበትን እንቅብ ከራሷ ላይ እንዳስቀመጠችው እየሮጠች ብትጮህም አልደረሰችበትም። ባቡሩ ፊኛውን እያስተነፈሰ መጎተቱን ቀጠለ። የኑሮዋን መኖ የያዘው የብረት ዘንዶ እየተምዘገዘገ ሲፈተለክ እጆቿን ወደ ሰማይ እያርገበገበች ተንበርክካ እንባ በተቀላቀለበት ድምፅ «ሽልንጌን ... ወይ ሽልንጌን» ሳታውቀው በሀዘኑ ጭነት ራሷን ስትደፋ የፍሬው እንቅብ ተንሸራቶ ከፊቷ ወደቀ። ፓፓያዎቹም እንደ እምቧይ እየተንከባለሉ በሀዲዱ ላይ ወደቁ።

አሚና ጠና ያለች የአርባ አምስት ዓመት ሴት ነበረች። የረር ጣቢያ አጠገብ ተወልዳ ለአቅመ ሄዋን እስክትደርስ ድረስ፣ ከቤተሰቦቿ ጋር ከብት እያገደች ስትኖር ከተዳረች ወዲህ፣ ባለቤቷ ከተማ ሄዶ የቀን ሥራ እየሠራ መኖርን ስለመረጠ ያላቸውን ከብቶች ሸጠው የረር በጭሰኝነት አንዲት ዳስ ሠርተው ተቀመጡ። ከጥቂት ዓመታት በኋላ ለጥቂት ጊዜ ታሰቃየው የነበረችው ወባ ባለቤቷን ነጥቃ ወሰደችው።

በባህላቸው መሰረት የባሏ ወንድም መጥቶ 'አግብቼ ልውሰድሽ' ቢላት፣ ከዘላንነቱ የከተማውን ሕይወት መርጣ ብቻዋን ቀረች። ከዚያም በኋላ ታናሽ እህቷ ፋጡማ ከባሏ ሸሽታ መጥታ ጥቂት ጊዜ አብረው ከኖሩ በኋላ "እዚህ መጥቶ ካገኘኝ ይገለኛል" ብላ ጥላት በባቡር ወደ ድሬዳዋ ወረደች።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አሚና ብቻዋን ትኖራለች። ዳሌዋ ሳይሟሽሽ፣ የደረቷ ፍሬ ሳይጠወልግ በፊት አብሮ አዳሪ ነበራት። በመጠኑም ጥቅም ታገኝ ነበር። ግን በመጨረሻ ካንዱ ከባቡር ዘበኛ ወንድ ልጅ ካገኘች በኋላ ዕድሜም ተጫናት፣ ፈላጊዋም ጠፋ። እሷና ልጇ አብርሽ ብቻቸውን ቀሩ። አብርሽ አምስት ዓመት ሲሆነው አክስቱ ፋጡማ መጥታ አባብላ ድሬዳዋ ወሰደችው።

ፋጡማ በድሬዳዋ የጥጥ ፋብሪካ ሠራተኛ ናት። በወር የምታገኘው ገቢ ሠላሳ ብር ብቻ ነበር። ከዚያ ውስጥ በየሳምንቱ አንድ አንድ ብር እቁብ ትጥላለች። በዚህ ሁኔታ ከሠላሳ ብር ደመወዝ ውስጥ አስቀርታ ባጠራቅመችው ገንዘብ ጨርቃ ጨርቅና ምግብ ለአሚና እና ለልጇ ይዛ መጣች።

ፋጡማ ኑሮዋ ከእጅ ወደ አፍ ቢሆንም ልጅ እንዲኖራት ትፈልግ ነበር። ግን እንደ እህቷ አልታደለችም። ስለዚህ አሚና ከነልጇ ወደ ድሬዳዋ ይዛት ሄዳ ሥራ ፈልጋላት አብረው እንዲኖሩ ብትለምናት፣ ለአሚና የረርን ለቅቆ መሄድ አልታይሽ አላት። በመጨረሻም «አንቺ እንኳን ባትሄጂ ልጅሽን ወስጄ ላስተምረው እኔ እንደምታዪኝ ልጅ የለኝም» ብላ ብትለምናት «እሱ እሺ ካለሽ ውሰጂው» አለቻት።

አሚና ምንም ቢሆን እኔን እናቱን ጥሎ አይሄድም። አልፈልግም ብሎ ይቀራል ብላ ተማምና ነበር የተናገረችው። ፋጡማ ግን አብርሽን ለሆዱ ባቀረበችለት ምግብና ለገላው ባለበሰችው ቆንጆ ልብስ እንዲሁም በዓይነ ህሊናው በሳለችለት የድሬዳዋ ከተማ ብልጭልጭነት አባብላ 'ከፋጤ ጋር እሄዳለሁ' ብሎ እናቱን ውጥር አድርጎ እንዲይዛት አስገድደችው። አሚና እምቢ ብትል እንኳን የልጁ ለቅሶ አፋጦ ያዛት። «ፋጤ ... ወጂን ዴምና።» እያለ አላስገባ፣ አላስወጣ አላት። መለየቱ የእናት አንጀቷን የሚቆርጠው ቢሆንም፤ ከሷ ጋር ተቆራምዶ ከሚኖር አክስቱ ጋ ድሬዳዋ ቢወርድ ቀን ይወጣለት ይሆናል ብላ በማመን ጨክና ወሰነች።

አንድ ቀን አቅፋው ካደረች በኋላ ማለዳ ጠዋት የአዲስ አበባ የሌሊት ባቡር ሲገሰግስ ደረሰ። ሦስት ቀን ብቻ እንድታርፍ የተፈቀደላት ፋጡማ ለእረፍቷ ማለቅ አንድ ቀን ሲቀራት ማታውኑ እቃዋን አደራጅታ፣ ገና ባቡር ሳይደርስ ነቅታ፣ ልብሶቿን ለብሳ፣ አሚናንም ቀስቅሳ ትጠባበቅ ነበር። የባቡሩ ድምፅ ገና ከሩቅ ከሀዲዱ እያስተጋባ ሲሰማ፣ አብርሽን ከእናቱ እጅ ላይ መንጭቃ ወሰደችው።

አብርሽ እንቅልፉን አልጠገበም ነበር። እናቱም ወደ ፉርጎው ውስጥ ሲገባ በፋጡማ እጆች ውስጥ እንዳለ ሲያዛጋና ዓይኖቹን ሲያሻሽ ተንጠልጥላ አቀፈችውና ሳመችው። "ልቀቂው ባቡሩ ተነሳ" ብላ መንጭቃው ወደ ውስጥ ገባች። በእናቱ ዓይን እንባ ሞላ። የባቡሩ ፊሽካ ከሩቅ የሚጮህ መሰላት። ከፊት ለፊቷ የብረት ቤት እየተምዘገዘገ አንዱ አንዱን እየተከተለ ሲያልፍ ህልም እንጂ እውን አልመሰላትም። ወዲያው ከፊቷ ባዶ ሲሆን ባነነች።
>>>
#ሽልንጌን
@ethiobooks
814 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:30:07 የሸዋሉል መንግሥቱ - 2 የመጨረሻው!
1.2K viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ