ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ ይጠበቃል ! የ በርሊን ማራቶን ዛሬ ከ ረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ መካሄድ ሲጀምር አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ አለም ሪከርድን ለ መስበር ውድድሩን ያካሂዳል ። በ ኬንያው ኢሉድ ኪፕ ቾጌ የተያዘው የ ማራቶን ሪከርድ በ አለም ሁለተኛው ፈጣኑ የ ማራቶን አትሌታችን ቀነኒሳ በቀለ በ ዛሬው ዕለት ይሰብረዋል ተብሎ ይጠበቃል ። ከ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በተጨማሪም ጉዬ አዶላ ፣ ታዱ አባተ ፣ ኦሊካ አዱኛ ፣ ተስፋዬ ሌንጮ እና ጌታዬ ገላው ሀገራችንን ወክለው በ ማራቶኑ የሚሳተፉ አትሌቶቻችን ናቸው ። መልካም እድል ለ ሀገራችን አትሌቶች 2.6K views04:35