#እንድታውቁት ከሚያዚያ 16 ጀምሮ በመላው አዲስ አበባ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅነት በ " ቴሌብር " ብቻ ተግባራዊ ይደረጋል ሲል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል። በ " ቴሌብር " ነዳጅ ስለ መቅዳት አሸከርካሪዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ነጥቦች ምንድናቸው ? ☞ በቅድሚያ የ " ቴሌብር "ተጠቃሚ መሆን፤ ☞ በቂ ክፍያ የቴሌብር አካውንት ውስጥ መኖሩን ማረጋገጥ፤ ☞ የ " ቴሌብር " የሚስጥር ቁጥርዎን ማስታወስና በአግባቡ መያዝ፤ የአከፋፈል ሁኔታው ምን ይመስላል ? ‣ የነዳጅ ማደያ ሰራተኞች የተጠቃሚውን ስልክ ቁጥርና የሚከፍሉትን የገንዘብ መጠን ሞልተው ሲጨርሱ የእርስዎ ስልክ ላይ የሚስጥር ቁጥርዎን እንዲያሥገቡ የሚጠይቅ አጭር መልዕክት ይመጣሎታል፤ ‣ በመቀጠል የሚስጥር ቁጥርዎን ከማስገባትዎ በፊት ከደረስዎት መልዕክት ላይ የተቀመጠ ገንዘብ መጠን ትክክል መሆኑን ያረጋግጡ፤ ካረጋገጡ በኃላ የሚስጥር ቁጥርዎን ያስገቡ፤ ‣ በመጨረሻም ክፍያው ከተፈፀመ በኃላ የክፍያውን ማረጋገጫ አጭር የመልዕክት ቁጥር ወዲያውኑ ይደርሶታል። የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ፤ የተሽከርካሪ ነዳጅ ግብይት ከሚያዚያ 16/2015 ዓ.ም ጀምሮ በ " ቴሌ ብር " ብቻ የሚፈፀም በመሆኑ ሁሉም አሽከርካሪ እንዳይጉላላ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል። ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ tikvahethiopia #Share @ethio_techs @ethio_techs 2.3K viewsBeki Hib Alex .Bl , 11:19