በአፋር ክልል ስምንት ሺህ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ሊመለሱ ነው፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ትምህርታቸውን አቋርጠው የቆዩ ስምንት ሺህ ተማሪዎች ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንደሚመለሱ የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። በክልሉ ሁለት ወረዳዎች (መጋሌ እና አባላ) ትምህርታቸውን አቋርጠው የቆዩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ የትምህርት ቁሳቁሶችን የማሟላትና ሼዶችን የመገንባት ሥራ እንደተሰራ የቢሮው ኃላፊ አብዱሀሰን ያዬ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡ #ለፈጣን እና ታማኝ መረጃ #share #share @ethio_schools @ethio_schools @ethio_schools 1.1K views11:07