Get Mystery Box with random crypto!

EOTC ቤተ መጻሕፍት

የቴሌግራም ቻናል አርማ eotclibilery — EOTC ቤተ መጻሕፍት E
የቴሌግራም ቻናል አርማ eotclibilery — EOTC ቤተ መጻሕፍት
የሰርጥ አድራሻ: @eotclibilery
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.08K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት
@Yesadikusitota
ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-30 21:41:06 ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 6
ስለ ቀሳውስት ይናገራል።

ቄስ ሚስቱ ብትወልድ ከአገልግሎት አይከልከል። ደም ካልነካው መቀደስ ይችላል።

ቄስ ወይም ዲያቆን እግዚአብሔርን አገለግላለሁ በማለት ከሚስቱ መለየት አይገባውም። ተባሕትዎ እይዛለሁ ወይም እመነኩሳለሁ ብሎ ሚስቱን ቢተዋት ከክህነቱ ይሻር።

በገበያ መካከል የሚበላ ቄስ፣ ከመሽታ ቤት ገብቶ የሚጠጣ ቄስ፣ ሞቶ የተገኘውን እና የአውሬ ትራፊን የሚበላ ቄስ ይሻር።

ከሌላ ቤተእምነቶች የሚገባ፣ ለሥጋዊ ፈውስ ለመፈወስ ብሎ ወደ ዓላውያን ወደ ከኃድያን የሄደ፣ ከሌላ ቤተ እምነቶች በዓል ተገኝቶ ያከበረ፣ ለቤተ እምነታቸውም እጅ መንሻ ያገባ ቄስ ይሻር።

ቄስ አንዲትን ሴት ያገባ ይሁን።
ቄስ ቂመኛ፣ ሰካራም አይሁን
ሠላሳ ዓመት ሳይሞላው ቄስ አይሾምም።

መጻሕፍትን ያልተማረ ይልቁንም አራቱን ወንጌል ያልተማረ ቅስና አይሾም።

የቄስ ሥልጣን ማስተማር፣ ማጥመቅ፣ መቀደስ እና መባረክ ነው።

ቄስ ምእመናንን አውግዞ መለየት አይችልም። ነገር ግን ችግር ያለበትን ሰው ወደቤተክርስቲያን እንዳይገባ መከልከል ይችላል። አውግዞ መለየት የጳጳሳት ድርሻ ነው። ቄስ ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይገባ፣ በምእመናን መካከል እንዳይገኝ መገዘት ነው የሚችል።

ቄስ ሐዋርያት ካስቀመጡት ቀኖና የወጣ በምእመናን ላይ አይጨምር።

አንድ ቄስ ከነበረባት ቤተክርስቲያን ወደ ሌላ ቤተክርስቲያን ሲሄድ አይቀበሉት። ኤጲስ ቆጶሱ ከፈቀደለት ብቻ ይቀበሉት።

ቀሳውስት ምእመናንን እንዳይቆርቡ መቆጣት አይገባቸውም። አንተ ገና ወጣት ነህ ወዘተ እያሉ መከልከል አይገባም። የሚከለክሉ ቢኖሩ ከሹመታቸው ይሻሩ።

ቀሳውስት ምእመናንን ይጠብቁ፣ አምስቱን አእማደ ምሥጢርም ጠንቅቀው ያስተምሩ።

ቄስ ወይም ዲያቆን ነውር ተገኝቶበት ከተሻረ በኋላ የክህነት ሥራ ደፍሮ ቢሰራ ከምእመናን ይለይ። ይህንን እያወቁ አብረውት ያገለገሉ ካህናትም ይሻሩ።

ቀሳውስት በአንቀጸ ኤጲስ ቆጶሳት የተናገርናቸውን መልካም ሥራዎች የሚሰራ ከዚያ የተከለከሉትንም የማይሰራ መሆን አለበት።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
362 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:36:27 ቤተክርስቲያንን በሁለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን #በትምህርት_ዕወቃት፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን #በኑሮ_ዕወቃት። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ።

በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ። እሊህም፦ ኪዳን ማስደረስ፥ ማስቀደስና ንስሐ ገብቶ መቁረብ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው።

ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ። በሕይወትህ ሁሉ ቤተክርስቲያናዊ ሁን!

#ርዕሰ_ሊቃውንት_አባ_ገብረ_ኪዳን
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
326 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:35:30 #ፍትሐ #ነገሥት #አንቀጽ #አምስት
ስለ ኤጲስ ቆጶሳት ይናገራል። ኤጲስ ቆጶስ:-
@ ጉቦ ከፍሎ የተሾመ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ከሹመቱ ይሻር። የሾሙት ኤጲስ ቆጶሳትም ይሻሩ።
@ ከሀገረ ስብከቱ ውጪ ክህነት የሰጠ ይሻር። ከሀገረ ስብከታቸው ውጭ የሚሾሙ ካህናትም ይሻሩ።
@ በዚህ ዓለም መኳንንት እንዲሁም ነገስታት ኃይልና እርዳታ የተሾመ ይሻር።በመንግስት ትእዛዝ የተሾመ ይሻር።
@ የኃጢኣተኛን ንሥሓ አልቀበልም የሚል ኤጲስ ቆጶስ ቢኖር ይሻር።
@ አራጣ የሚቀበልና ነገር ሰርቶ ሰውን ከሰው የሚያጣላ ይሻር።
@ ዝሙት የሰራ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ይሻር።
@ ዓለማዊ ሥራን የሚሰራ ጳጳስ ከሹመቱ ይሻር።
@ 50 ዓመት የሆነው ሰው ይሾም። 50 ዓመት የሆነው ባይገኝ ለሹመት የበቃ ሆኖ ከተገኘ ከ50 ዓመት በታች ያለውንም ይሹሙት
@ ፓትርያርኩ ሳይጽፉለት ወይም ሳይፈቅዱለት ወደ ንጉሡ የሄደ ጳጳስ ይሻር።
@ ለመፈራት ብለው ሰውን የሚደበድቡ ወይም የሚማቱ ቀሳውስት ዲያቆናት እና ጳጳሳት ይሻሩ።
@ የጠንቋዮችን ነገር አምኖ የሚቀበል እንዲሁም ኮከብ ቆጣሪ እና ለጥንቆላ ቅጠል የሚበጥስ ይሻር።
@ ከሐራጥቃ ጥምቀትን የተቀብለ ወይም የቆረበ እንዲሁም በቦታ ከእነርሱ ጋር የጸለየ ይሻር።
@ ኤጲስ ቆጶሳት የተሾሙበትን ሀገረ ስብከት ትተው በሌላ ቦታ የትንሣኤን በዓል ካከበሩ ይሻሩ።
@ ሁለት ጊዜ የተሾመ ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን ይሻር።
@ ቆሞስ የኤጲስ ቆጶስ ተወራጅ ነው። በኤጲስ ቆጶስ ትእዛዝ መሰረት ይሰራል።


@ ኤጲስ ቆጶስ ቀሳውስትን ይባርክ እንጂ እርሱ በቀሳውስት አይባረክ። የክርስቶስን ሥጋውን ደሙንም ከኤጲስ ቆጶሳት ይቀበል እንጂ ከቀሳውስት አይቀበል።
@ የኤጲስ ቆጶሳት ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን። ይኽውም ጥቅምት 12 እና ከትንሳኤ በኋላ በ28ኛው ቀን ነው። በጉባኤውም አንድ መጽሐፍ ቅዱስ በአንድ ወንበር ይቀመጥ
@ ኤጲስ ቆጶስ የተቸገሩትን ይርዳ። ሕዝቡ እየተራበ እየተቸገረ እርሱ ማእደ ሥጋውን የሚያሳምር አለባበሱን የሚያስጌጥ ጳጳስ አይባልም።
@ መሥዋእት ሠው ተው ጸሎት ጸልየው ወደ እግዚአብሔር የሚያማልዷችሁ ናቸውና ኤጲስ ቆጶሳትን አክብሩ።
@ በቀለኛ ጳጳስ ጳጳስ አይባልም።
@ በቅዳሴ ጊዜ የኤጲስ ቆጶሱን ሥም ይጥሩ።
@ ኤጲስ ቆጶሳት የበደለውን ይገሥጹ
@ ኤጲስ ቆጶሳት ያልተማሩትን ያስተምሩ ያመኑትን ያጽኑ።
@ ኤጲስ ቆጶስ ሆይ ሽማግሌዎችን አረጋጋቸው እንጂ አታሳዝን።
@ ኤጲስ ቆጶስ ሆይ ሽማግሌዎችን እንደ አባትህ ደስ አሰኛቸው። ወጣቶችን እንደ ወንድሞችህ እያቸው። ቆነጃጅትን እንደ እህቶችህ እያቸው። ባልቴቶችን እንደ እናትህ እያቸው። እናት አባት የሌላቸውንም እንደ እናት እንደ አባት ሆነህ ደስ አሰኛቸው።
@ ኤጲስ ቆጶስ አንዱንስ እንኳ ሳይመረምር መሾም የለበትም።
@ ኤጲስ ቆጶስ ከንቱ የሆነ የዚህን ዓለም ነገር አይስማ።


@ ኤጲስ ቆጶስ የላመ የጣመ አይቅመስ። የሞቀ የደመቀ አይልበስ።
@ ኤጲስ ቆጶስ ነዳያንን እየጠላ ባለጸጎችን አይውደድ።
@ ኤጲስ ቆጶስ ወደ አሕዛብ በዓል አይሂድ። በአነጋገር በሥራ ለምእመናን አርዓያ ይሁን።
@ ኤጲስ ቆጶስ ልቡ እንዳይገዝፍ ሥጋ አይብላ። ጽኑ ደዌ ከታመመ ግን ዓሣ ይብላ። ወይንም ጥቂት ይጠጣ።
@ ራሱን የሰለበ ሰው ኤጲስ ቆጶስና አይሾም። በግድ ሌሎች ሰልበውት ከሆነ ግን ከሹመት አይከልከል።
@ ኤጲስ ቆጶስ ከተሾመ በኋላ ሶስት ሱባኤ ይጹም።
@ ዕውር፣ መናገር የማይችል፣ መስማት የማይችል፣ ኤጲስ ቆጶስነት አይሾም።
@ ኤጲስ ቆጶስን ቢገኙ ሦስት ባይገኙ ሁለት ኤጲስ ቆጶሳት ይሹሙት።
@ ኤጲስ ቆጶስናን ድንግልና ከምንኩስና ያለው ሰው ይሾም። ቢታጣ ግን ሕዝባዊ ይሁን
@ ኤጲስ ቆጶስ ለሰው የሚያዝን የሚራራ፣ ልቡናው ከቂም ከበቀል ከክሕደት የተለየ፣ በበጎ ሥርዓት ሁሉ የጸና ይሁን።

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
336 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:39:23
509 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:39:19
427 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:39:14
357 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:39:07
361 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:39:02
352 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 12:58:57
በዛሬው ዕለት መምህራችን አባ ገብረ ኪዳን ግርማ በብጹዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ ርዕሰ ሊቃውንት መምህር አባ ገብረ ኪዳን ግርማ በሚል የማዕርግ ስም እየተጠሩ የርዕሰ አድባራት ወገዳማት ጣና ቂርቆስ ገዳም የ4ቱ ጉባኤያት (ብሉያት፣ ሐዲሳት፣ ሊቃውንት፣ መነኮሳት) ምስክር መምህር ሆነው ተሹመዋል።
ክርስቲያኖች እንኳን ደስ አላችሁ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
555 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 10:14:44 እንዳይፈረድብህ በባልንጀራህ ላይ አትፍረድ

በአንድ ወቅት በግብጽ ገዳማት አንድ ወጣኒ መነኩሴ “ጥፋት አጠፋ፣ ሥርዓተ ገዳም አፋለሰ” ተብሎ መናንያኑ ጉዳዩን እንዲያዩና እንዲወስኑበት ከየበአታቸው ተጠሩ፡፡ ከተጠሩት መነኮሳት መካከል አንዱ ጥቁሩ ኢትዮጵያዊው ሙሴ ጸሊም ነበር፡፡ እርሱም ሁሉም ከተሰበሰቡ በኋላ ዘግይቶ በተቀደደ አቁማዳ አሸዋ በጀርባው አዝሎ አሸዋውን ከኋላው እያፈሰሰ መጥቶ በመሃላቸው ተገኘ፡፡

የተሰበሰቡት መነኮሳትም አባ ሙሴን ይህን ስለምን አደረግከው ብለው በጠየቁት ጊዜ በሀዘን ተውጦ “በጀርባዬ የማላያቸውን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኃጢአቶቼን ተሸክሜ ሳለሁ በወንድሜ ለመፍረድ መጥቻለሁ” አላቸው፡፡ መነኮሳቱም እጅግ ተጸጸቱ፡፡ ጉባኤውም ፍርዱን ትቶ ተበተነ፡፡

“እንዳይፈረድብህ በባልንጀራህ አትፍረድ” የሚለውን የወንጌል ቃልም በተግባር አስተማራቸው፡፡ልብን በሚነካ በዚህ በጎ ትምህርቱም መነኮሳቱን ከመፍረድ ሃጢአት ታደጋቸው፡፡
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
463 viewsNigatu Ye Enatu Lij, 07:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ