የሐዋርያት የሃይማኖት መግለጫ አንቀጽ ፩ እኔ ሁሉን በሚችል፣ ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በእግዚአብሔር አብ አምናለሁ፡፡¹ አንቀጽ ፪፦ ደግሞም በአንድ ልጁ² ፣ በመንፈስ ቅዱስ በተፀነሰ፣ ከድንግል ማርያም በተወለደ³ ፣ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን መከራን በተቀበለ⁴ ፣ በተሰቀለ⁵ ፣ በሞተ እና በተቀበረ፤ ወደ ሲዖልም በወረደ፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን በተነሣ፡፡⁶ ወደ ሰማይም በወጣ ሁሉን በሚችል በእግዚአብሔር አብ ቀኝ በተቀመጠ⁷ ፣ ከዚያም በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ በሚመለስ፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ፡፡⁸ አንቀጽ ፫፦ ደግሞም በመንፈስ ቅዱስ⁹ ፣ በአንዲት ቅድስት የሐዋርያት ቤተክርስቲያን ፣ በቅዱሳን አንድነት¹⁰ ፣ በኀጢአት ስርየት¹¹ ፣ በሥጋ ትንሣኤ¹²፣ በዘላለም ሕይወት አምናለሁ፡፡¹³ አሜን! የመጽሐፍ ቅዱስ ማጣቀሻዎች ¹ ራዕ ፬÷፲ ² ፩ ዮሐ ፬÷፱ ፤ ዮሐ ፩÷፲፰ ³ ማቴ ፩÷፲፰፣፳፤፪÷፲፩ ፤ ሉቃ ፩÷፳፯፣፴፬ ⁴ ሐዋ ፬÷፳፯-፳፰ ፤ ማቴ ፳፯÷፪ ⁵ ማቴ ፳፰÷፭ ፤ ፩ ቆሮ ፩÷፳፫ ⁶ ዮሐ ፲፱÷፴፫ ፤ ፪ ቆሮ ፭÷፲፬-፲፭ ፤ ፩ ቆሮ ፲፭÷፫ ፤ ሐዋ ፪÷፳፯ ፤ ፩ ተሰ ፬÷፲፬ ፤ ሮሜ ፰÷፴፬ ⁷ ዮሐ ፫÷፲፫ ፤ ኤፌ ፬÷፲ ፤ ማር ፲፮÷፲፱ ፤ ሉቃ ፳፬÷፶፩ ፤ ሮሜ ፰÷፴፬ ፤ ቆላ ፫÷፩ ፤ ዕብ ፩÷፫፣፰÷፩፣፲÷፲፪፣፲፪÷፩-፪ ፤ ፩ ጴጥ ፫÷፳፪ ⁸ ፪ ጢሞ ፬÷፩ ፤ ሐዋ ፲÷፵፪ ⁹ ሐዋ ፲÷፴፰፣፩÷፭፣፪÷፴፫፣፲፫÷፪ ፤ ዮሐ ፲፬÷፳፮ ፤ ቲቶ ፫÷፭ ¹⁰ ሮሜ ፲፪÷፭ ፤ ቆላ ፩÷፲፰ ፤ ኤፌ ፭÷፳፯፣፬÷፲፪-፲፫፣፪÷፳ ፤ ፩ ቆሮ ፲፪÷፳፰ ፤ ዮሐ ፲፯÷፲፩-፳፫ ¹¹ ማቴ ፳፮÷፳፰ ፤ ሐዋ ፲÷፵፫፣፲፫÷፴፰-፴፱ ፤ ኤፌ ፩÷፯ ፤ ቆላ ፩÷፲፫-፲፬ ¹² ፩ ቆሮ ፲፭÷፲፪-፶፰ ¹³ ዮሐ ፲፯÷፪-፫፣፫÷፴፮፣፭÷፳፬፣፮÷፵ ━━━━⊱✿⊰━━━━ @elgraceministry @elgraceministry 768 viewsሱራፌል ወርቁ ጸጋ, 19:47