Get Mystery Box with random crypto!

#update በትላንትናው እለት እስራኤል እና ስዊዘርላንድ የመጀመሪያዉን የጦጣ ፈንጣጣ (Mon | Health. Com/ጤናን በቴሌግራም

#update

በትላንትናው እለት እስራኤል እና ስዊዘርላንድ የመጀመሪያዉን የጦጣ ፈንጣጣ (Monkeypox) በሽታ ሪፖርት አድርገዋል።

ባለፉት ሳምንታት በእንግሊዝ፣ በፈረንሳይ፣ በጀርመን፣ በቤልጂየም፣ በጣሊያን፣ በፖርቹጋል፣ በስፔን እና በስዊድን እንዲሁም በአሜሪካ፣ በካናዳ እና በአውስትራሊያ ከ100 በላይ የጦጣ ፈንጣጣ በሽታ(Monkeypox) መገኘቱን ተከትሎ ቫይረሱ ሊስፋፋ ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።

ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ቫይረሱ በሌለባቸው አገሮች ውስጥ ያለው ወረርሽኝ ያልተለመደ እንዲሁም የአሁኑ የጦጣ ፈንጣጣ(Monkeypox) ዝርያ የሚለየዉ በግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚተላለፉ ኢንፌክሽኖች ሊሆን እንደሚችል እየተገለፀ ይገኛል።

የዓለም ጤና ድርጅት በበሽታው ከተጠቁ ሀገራት እና ከሌሎች ጋር በመሆን የበሽታ ክትትልን በማስፋት የተጠቁ ሰዎችን ለማግኘት እና ለመደገፍ እንዲሁም በሽታውን እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል መመሪያ ለመስጠት እየሰራ እንደሆነ ገልጿል።

የዝንጀሮ በሽታ ከኮቪድ-19 በተለየ ሁኔታ ይተላለፋል። ሆኖም ግን በንክኪ ከሰዉ ወደ ሰዉ ሊተላለፍ ስለሚችል ጥንቃቄ ይሻል ።

እንደ የዓለም ጤና ድርጅት ገለፃ በሚቀጥሉት ሳምንታት በርካታ የአዉሮፓ ሀገራት የጦጣ ፈንጣጣ በሽታ ሪፖርት ሊኖር እንደሚችል ገልጿል።
#Dr. Haileleul