የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን | Ethiopian Catholic Charismatic
የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ
የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም።
በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል
6ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ
“ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።”
— ሐዋርያት 1፥8
አንድ ሰው ትክክለኛ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ሲያገኝ በሕይወቱ ላይ የሚታዩ የለውጥ ምልክቶች በጥቂቱ
1 ለፅድቅ ሕይወት ልዩ ቦታ መስጠት
2 አዲስ የፀሎት ሕይወት ልምምድ
3 የእግዚአብሔርን ቃል መረዳት (መገለጥ)
4 ከማይጠቅመው ነገር ይለያል
5 የመመስከር ድፍረት ያገኛል
6 ዓለማዊነትን የማሸነፍ ጉልበት ያገኛል
በዚህ ርዕስ ላይ ምሽት 3:30 ጀምሮ ፀሎትና ውይይት ይኖረናል።