የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን | Ethiopian Catholic Charismatic
የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ
የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም።
በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል
5ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ
“በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።”
— ዮሐንስ 15፥7
በእግዚአብሔር የሚኖር የእግዚአብሔር ቃል እንዲኖርበት የፈቀደ ሰው ሁልግዜም የምስጋና ሕይወት አለው። ፀሎቱ እንደተሰማ ስለሚረዳ በምስጋና ይኖራል።
እግዚአብሔር ሆይ ትውልድ የአንተን ቃል ተረድቶ እንዲኖር እንፀልያለን።