Get Mystery Box with random crypto!

ዲያቆን ሞገስ አብረሃም|moges abreham

የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconmoges17 — ዲያቆን ሞገስ አብረሃም|moges abreham
የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconmoges17 — ዲያቆን ሞገስ አብረሃም|moges abreham
የሰርጥ አድራሻ: @deaconmoges17
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 472
የሰርጥ መግለጫ

እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህ ቻናል በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ እና በተለያዩ ጊዝያቶች ያዘጋጀዋቸውን ኦርቶዶክሳዊ መጣጦፎች ጽሑፎች እና የመጻሕፍት ዳሰሳዎች መማርያ ይሆኑ ዘንድ የማጋራበት ይሆናል።
https://t.me/Mogesabreham
https://t.me/joinchat/AAAAAEczV7heeRJD86ok2g

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-28 16:45:25 በቤተክርስቲያን የራሳችን ስንፍና ያደክመን ይሆናል አንጂ አድካሚ መጸሐፍ አለ ማለት አይደለም። ነገር ግን የምንጽፍባቸው ስልቶች ካለው የኖሩ ውጣ ውረድ ጋር ተደምሮ ሊያደክሙ ግን ይችላሉ። ዛሬ መጻሕፍት ሚነበቡት በእረፍት ሰዓት አልያም በትርፍ ጊዝያት ነው። ስለዚህ ሰው አረፍ ብሎ ሲያነብ የበለጠ እንዲደክመው ከማድረግ ይልቅ እረፍቱን ይበልጥ እንዲወደው ማድረግ ትልቅ ጥበብ ነው። የጸሐፍያን ምክንያተ ጽሕፈት ይለያያል አንድ አንድ ጸሐፍያን ሁሉም ምእመናን ተደራሽ እንዲሆኑ በማሰብ አንድ አንድ ጸሐፍያን ደግሞ የተፈጠሩ ታሪካዊ ዶግማዊ ቀኖናዊ ክፍተቶችን ለመድፈን ብቻ ጠጠር ያሉ አገላለጾች በመጠቀም የሚጽፉ ይኖራሉ። በምክያታቸውን በያዙት አጀንዳ ልክ የሥነ ጽሑፍ ስልታቸው ይለያይ ይሆናል። ነገር ግን በቤተክርስቲያን ውስጥ ላለው አካል ሁሉ መረዳት በሚመች መልኩ ጽፎ ማቆየት ምን አልባት አሁን ካለው የንባብ ፍላጎት ማነስ አንጻር ትልቅ መፍትሔ ነው። ብዙም ሳያጠቁር ብዙም ሳያነጡ ጠየም አድርጎ መጻፍ አንባቢውን የማያደክም የመሆን እድሉ ከፍ ያለ ነው። የብርሃን እናት የተሰኘው መጸሐፍም አንባቢ አንዲ ከጀመረው በዛው ሊያገባድደው በሚችልበት ሆኔታ የተጻፍ የስነጽሑፍ ስልት ይመስለኛል።

፯:-መነሻውን የሚያውቅ መዳረሻ

አንድ አንድ ጊዜ የጽሖፎች ጭብጥ ሐሳብ ላይ ለመድረስ እጅግ አዳጋች የሆኑ ጽሑፎች ይኖራሉ። የዋናው ሀሳብ መንደርደርያ የሚሆኑ ጥልቅ የሆኑና የምንፈልገውን ርእሰ ጉዳይ አንባቢው እንዲረዳልን የሚያደርጉ ሐተታዎች አስፈላጊ ናቸው። የብረሃን እናት መጸሕፍም ዋናው ጉዳዩ እንዲሁም ሊገልጥ የፈለገው "እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ነው" ነገር ግን የእርሷን ነገር ከመዘርዘሩ አስቀድሞ ከእርሷ በፊት የነበሩትን አነሳ። መጸሐፉ ከእናቷ ሔዋና ከአባቷ ከአዳም ተንደርድሮ ይመጣና ዋናውን ነጥብ ያገኘዋል። አስተውለን ከሆነ ውዳሴ ማርያም የመጀመርያው የምስጋና ክፍል ላይ ስለ እመቤታችን ነገር ብዙ አያነሳም። በዚህ በመጀመርያ ምስጋና ቀን አዳምና ሔዋንን ደጋግሞ ነው ሚያነሳው ስለዚህም ይመስላል የእመቤታችን ክብር የሚገልጥ ሰው ከአዳምና ከሔዋን መጀመሩ ግድ መሆኑን እናስተውላለን። መምህር ሄኖክ ኃይሌም በመጸሐፉ እጅግ ደስ በሚል ሁኔታ የአዳምንና የሔዋንን ነገር በተለያዩ ርእሶች ይዞቸው ከመጣ በኋላ መዳረሻው ወደሆነችው ወደ እመቤታችን ይገባል። ስለዚህ መነሻውንም መዳረሻውንም በእኩል መንገድ ያገናኘ የአጻጻፍ ስልት ጎልቶበታል ብዬ አምናለው።

፰:-መንፈሳዊ እይታዎች

የቅዱስ ዮሐንስ አፈውርቅን ጽሑፎች ስናነብ የሚደንቀን አንድ ቁም ነገር አለ ይህ አባት ምናቀውን መጸሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ ለትምህርቱ ሲጠቀምባቸው እለት እለት ከምናስበው ወይም ከምናቀው ውጪ አዲስ እይታዎችን ያሰቃኘናል። በዚህ ተገርመን እናነበዋለን። መምህር ሄኖክም በብዙ ጽሑፎቹ ይሄንን መንገድ ያሳየን ይመስለኛል። የቤተክርስቲያኒቱን መሠረተ እምነት እስካልነካ ድረስ ሰዎች ወደተሻለ የአረዳድ ደረጃ የሚወስዱ እይታዎችን መጠቀሙ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ። ነገረ ማርያምን መአከል ተደረገው የተጻፉ መጸሐፍቶች አሉ እነሱም የራሳቸው ጠንካራ ጎን አላቸው የብርሃን እናት የተሰኘው መጸሐፍ ግን በሚያነሳቸው ጉዳዮች ሁሉ በጥሩ አገላለጾች የተቃኙ እና አዲስ እይታዎች ስላየውበት በግሌ ምቾት ሰጥተውኛል።

፱:-ተያያዥና አንኳር ጥያቄዎች ማቅናት

ከመጸሐፉ ሽፈን ጀረባ ላይ ያሉ ጥያቄዎች ውስጥ አንድ አንዶቹ እለት እለት ምናስባቸው አልያም የሚጠየቁ ጥያቄዎች ናቸው። ከዕጸ በለስ ከነጻ ፈቃድ እና ከመሰል ጉዳዮች ጋር የሚነሱ እና ሌሎች ጥያቄዎችን በምሳልያዊ አገላለጽና ከሊቃውንቱ ማመሳከርያ ጋር በማድረግ ምላሽ ይሰጥባቸዋል። ከተነሳበት ሐሳብ ጋር ተዛምደው የተነሱ ሐሳቦችን እያቀና ምላሽ ይቸራል። ለምሳሌ የአንድን ዛፍ ፍሬ መብላት የሰውን ልጅ ይኼንን ያህል ዋጋ ማስከፈል ነበረበት? እግዚአብሔርስ ከመጀመርያው ዛፉን ለምን ፈጠረው ? ከፈጠረው በኋላስ ለምን እንደይበሉ ፈለገ? ከሚከለክላቸው ለምን ዛፉን አያጠፋውም? የሚሉና ከ10 በላይ የሚሆኑ መሰል ተያያዥ ጥያቄዎችን አንስቶ ይጠቀልላል።

፲:-ነገረ ማርያምን በአዲስ አቀራረብ

ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በመሠረተ እምነቷ አስገብታ ከምትሰጣቸው ትምህርቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ነገረ ማርያም ነው። ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ይህንን የቀና ትምህርት ይበልጥ ለማጎላት በዛ ያሉ ትምህርቶች እና መጸሐፉች ተበርክተዋል። በአቀራረብ ደረጃ ግን ተመሳሳይ የአጻጻፍ ስልት እና አቀራረብ ያላቸው መሆኑን እናስባለን። የብርሃን እናት የተጻፈበት የሥነጽሐፍ ስልቱ በራሱ ለነገረ ማርያም ትምህርት ሌላ መልክ ሰጥቶታል። ነገረ ማርያም መጸሐፍ ቅዱሳዊ መነሻ እንዳለው ከምናስቀምጣቸው ዋና ዋና ክስተቶች መካከል የቅዱስ ገብርኤል ብሥራት የኤልሳቤት ምስጋና የእመቤታችን የራሷ ጸሎት ተጠቃሽ ነው። ይህንንም የጻድቅን ቀጠሮ በሚለው በአራተኛው ምዕራፍ እና የምሕረት አዋጅ በሚለው በሁለተኛው ምዕራፍ ላይ እነዚህ መጸሐፍ ቅዱሳዊ ሐረጋት ተተንትነዋል። የዝምተኛዋ ንግግሮች በሚለው ርእስ ውስጥ የተነሱ ማብራርያዊ ነጥቦች ብቻ አብስለን ካየናቸው ለነገረ ማርያም ትምህርት እጅግ ማመሳከርያ ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው። ከሁሉ ይልቅ ነገረ ማርያም ትምህርት ላይ በማወቅም ባለማወቅም ለሚስቱ ሰዎች ከኤልሳቤጥ ከቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችን ጸሎት ያልወጣ ትምህርት አለመሆኑን ያሳየበት ነው። ስለ እመቤታች በብዙ እየተደነቀ የሚገልጻቸው ነገሮች ሁሉ ልብን ይስባሉ።

(ብዕር ያለምልም። ላዘጋጁ ለመምህር ሄኖክ ኃይሌም ምክንያት ድኅነት የሆነች እመቤታችንን ይበልጥ እንድናመሰግናት ምክንያት ስለሆነን ጥበብ አብዝቶ እውቀት አስፍቶ ይስጥልን እያልኩኝ። ይህንን መጸሐፍ በማንበብ አውቆ ወደ መደነቅ አንብቡ እራስን ወደ መመርመር የሚያደርሰውን ጸጋ እንካፈለ እላለው)

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
20/10/2014
259 viewsMoges abreham, 13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 16:45:25 +++++የብረሃን እናት+++++
(አጭር መጸሐፋዊ ቅኝት)(የንባብ ጥቆማ)
"ብርሃንሽም ከፀሐይ ብርሃን ይበልጣል"

መምህር ሄኖክ ኃይሌ የብርሃን እናት ብሎ ያዘጋጀው መጸሐፍ ሥነ ጽሑፉዊ ውበቱ የተጠበቀለትና በተለይ በተመስጦ ሊነበብ እና ሊያስተምር የሚችል አገላለጾችና የአጻጻፍ ስልቶች ያየሉበት ይመስለኛል ለአብነትም ጥቂቱን የመጸሐፉን ጠንካራ ጎን በተረዳውበት መስክ ልግለጥ።

፩:-አንባቢውን የትምህርቱ መአከል ማድረግ

እግዚአብሔር በቃለ መጻሕፍት ብዙ ይናገራል። ዓለሙን ሁሉ ብታተርፍ ነፍስህን ግን ብታጎድል ምን ይረበሐል ሚለውን የመጸሐፍ ቃል ተጠቀመው የመነኑ ስንቶች ናቸው። ለዚህም ነው የትኛውም አይነት መንፈሳዊ ድርሰት አማኙ የሚገለጥበት አንባቢው በሕይወቱ የሚተርጉምበት የእግዚአብሔር ማስተማርያ መንገድ ነው የምንለው። የብርሃን እናት የተሰኘው መጸሐፍ አንድ አንድድ ቦታ ላይ ትንታኔውን ገታ እያደረግ አንባቢው ወደ ራሱ እንዲመለከት እድል ይሰጣል። ምክንያቱም የመጻሕፍት ዓላማ ሕይወት መሆን ጭምር እንጂ ማቀበል ብቻ አይደለም። የብዙ አበው ታሪክ በመጸሐፍ ሰፍሮልን የምናገኘው እንደው እነርሱን ለማወቅ ብቻ ሳይሆን በእነርሱ መወደቅና መነሳት ውስጥ ራሳችንን እንድናይ መሆኑን ልብ እንበል። በዚህም ረገድ መምህር ሄኖክ ኃይሌ በጽሑፎቹ ውስጥ አንባቢው እኔስ የሚል ጥያቄ እንዲፈጥር የሚያደርጉ አገላለጾችን ይጠቀማል። አንባቢውን መአከል የሚያደርገውም በጥያቄም በምክር ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ አንዱን ለመጥቀስ ከሔዋን ጋር ሲነጋገር ስለነበረው ስለ ዕባብና ስለ ዕጸ በለስ ከተነተነ በኋላ እንዲህ ይላል።

"ወዳጄ ይህን መጸሐፍ ማንበብህን ቆም አድርገህ የአንተን እባብ የአንተን ዕፀ በለስ ለይተህ አስብ በፍጹም በየትኛውም መንገድ በእኔ ሕይወት እባብ መጥቶ በጭራሽ አያውቅም ካልከኝ ደግሞ ትንሽ ዞር ዞር በልና አንተነትህን ከዚሁ ታሪክ ውስጥ አብረን እንፈልገው።........"


፪:-ርእሰ ጉዳዮችን በጥያቄ መልክ ማስተላለፍ

ሐሳቦችን በጥያቄ መልክ መግለጽ በተለይ በጥንት ሊቃውንት አጻጻፍ ውስጥ የተለመደ ይመስላል። በተለይ ለመደነቅና ለአንክሮ የሚጠቀሙበት ስልትም ነው። እግዚአብሔር እና ሥራውን ሌሎች ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎችን አልያም አስደናቂ ክስተቶች ላይ በጥቅሉ ከቃል በላይ ለሆኑ ነገሮች ይህንን የአጻጻፍ ስልት አሁን ላይ በስፋት ባንመለከተውም መጠቀም የተለመደ ይመስለኛል። የብርሃን እናት መጸሐፍም በየንዑስ ርእሶች ውስጥ ተደንቆ አንባቢውን ወደመደነቅ የሚያደርስበትን በጥያቄ ምልክት የተዘጉ ትንታኔዎች አሉት። ይህ ጥያቄ የታሪኩን ባለቤት ጭምር ነክቶ ያልፉል። ለምሳሌ ሔዋንና አዳምን ገጽ ለገጽ እንደሚያናግር ሰው ስለምን በደላችሁን እያለ ፍቅራዊ ወቀሳ ሲያቀርብላቸው የምናቀው ቅዱስ አትናቴዎስን ነው። በዚህ መጸሐፍ ላይም አዳምና ሔዋንን ፍቅራዊ ጥያቄ ሲጠይቅ እንመለከታለን። በሌሎች ክፍሎች ላይ እንደተነሳበት አንባቢው ልቦና ላይ ወይ መደነቅ አልያም ልንጠይቃቸው የሚገቡትን ሁሉ እየቀደመ ይጠይቃል። ለአብነትም ሔዋንን በመጀመርያ ምዕራፉ ብዙ ያናግራታል አንድም ያነሳሳታል ስለእርሷ ሚገባውን ሁሉ ይገልጻል ቆየት ብሎ ደግሞ የትውልዱን ጥያቄ ያነሳል።

"አምላክነትን የሚያስመኝ ገዢ ሆነሽ በተፈጠርሽበት ዓለም የጎደለብሽ ምን ነገር ነበር? ገነት ውስጥ እየኖርሽ የምኖርበት ቦታዬ ይበቃኛል ማለትን እንዴት አልቻልሽም? የሰው ልጆች ሁሉ እናት የመሆን ክብር ተሠጥቶሽ ሳለ ለልጅ ልጆችሽ ሕመምና ሞትን ያወረስሽን ለምንድር ነው? ገነት ከምታህል ርስት ወጥተሽ በተረገመች ምድር የወለድሽንስ ስለምንድነው? የሚል የብዙ ትውልድ ጩኽት በሕሊናው የሚጮኽባት ሔዋን ብቻ ነች"

፫:-ርእስ የንባብ በር ነው

ለጽሑፎች የሚሰጡ ርእሶች አሁን ላይ በጣም ወሳኝነት አላቸው። እጅግ የለመድናቸውን ታሪኮች ምን አልባት ርእሳቸው ስቦን እንደ አዲስ ተመስጠን ምናነብባቸው ጊዜ አለ። ለምሳሌ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ የሕማማት መጸሐፉን ጨምሮ አሁን ያለው የብርሃን እናት የተሰኘው መጸሐፍ ላይ ይህንን ርእስ አሰጣጥ ሲያስለምደን እናየዋለን። ርእሶቹ ለንባብ የሚገፋፉ እና እጅግ ሳቢዎች ናቸው። የወደቀው መልአክ በሚለው ፈንታ የሰማዩ ይሁዳ በሚል ስለ ፈታኝ ዲያቢሎስና ተዛምዷዊ ሀሳቦችን ያነሳል። አዳምና ሔዋን ነጻ ፈቃድ አላቸውን? ከሚለው ይልቅ የነጻነት እስረኞች በሚል የተተካ ብዙ ጥያቄዎች የተመለሰቦት አስተማሪ ምሳሌዎች ያሉበት ክፍል አለ። ብሥራተ ገብርኤል አልያም አብሳሪው መልአክ ከሚለው ይልቅ የሰማዩ ንስር በሚል እመቤታችንን በቅዱስ ገብርኤል አንጻር ይናገርላታል ። መጥምቁ ዮሐንስ በማኅጸን ሆኖ ስለሰጠው ክብር የሚያነሳውን ሐተታ ደግሞ "ያልተወለደው ባለቅኔ" በማለት ይዞታል። ዘመኑ መጸሐፍ ሲያነብ መጀመርያ ማውጫውን ከዛን ደግሞ ከጀርባ የተሰጡ አስተያየቶችን ይመለከታል። ስለዚህ አይቶ የሚዘጋውን ርእስ ከመስጠት አይቶ ምን ማለት ይሆን ብሎ ለማንበብ የሚጥርበትን ሳቢ ርእስ መስጠት ለአንባቢ ተደራሽ መሆን ነው ብዬ አስባለው።

፬:-የርእስና የሐተታ ተዛምዶ

አንድ መጸሐፍ እጅግ ጥሩ ርእስ ኖሮት ሐተታው ግን ደካማ ከሆነ ብዙ አመርቂ ላይሆን ይችላል። አንድ አንድ ጊዜ ለእያንድ አንዱ ክፍሎች የተሰጡ ርእሶችን ተመልክተን በጉጉት ወደሐተታ ስንገባ ወይ በድንብ አልተገለጸም አልያም ደግሞ የአጻጻፍ ስልቶ ቦዙ ግልጽ ላይሆን ይችላል። ትልቁ ነገር ሐተታ ከሚሰጠው ርእስ ጋር እኩል ውበት ሊኖረው ይገባል። መምህር ሄኖክ ኃይሌም በመጸሐፉ ለርእሱ ታማኝ መሆኑን ያሳየበት የአጻጻፍ ስልት ተጠቅሟል። ርእሱን ሚያጠናክሩ በዛ ያሉ ርእሰ ጉዳዮችን ቢዳስስም መደምደሚያው ግን የርእሱ ጭብጥ ሀሳብ ነው። በጥቅሉ ለመቃኘት ሳስብ ርእሱ ከሐተታው ጋር ደስ በሚያሰኝ ገለጻ ተዛምደዋል። ለምሳሌ ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮኮብ በሚለው እጅግ ሳቢ ርእስ ውስጥ ብዙ ያልተነገረለት አረጋዊው ዮሴፍ ተጉግጿል። ርእሱ ዮሴፍንካሰተዋወቀበት ትንታኔ ጋር ያለውን ዝምድና ማውሳት ይቻላል።

፭:-ሊቃውንትንና መጻሕፍትን ማናገር

በየዘመኑ የተነሱ ከሀገር ውስጥም ውጪም ያሉ ሊቃውንት ያላስተማሩበትና ያልጻፉበት ርእስ ጉዳይ ማግኘት እጅግ ከባድ ነው። እነዚህን በእውቀትም በሕይወትም የበረቱ ሊቃውንትን አሁን ላለው አንባቢ በአንድም በሌላም አድርጎ ንግግራቸውን ማስነበብ ብልህነት ነው ትርጓሚያችንም ቢሆን ለሐተታው ማረጋገጫ "እንዲል" እያለ የመምህራንንና የመጻሕፍትን ማመሳከርያ ያቀርባል። የብርሃን እናትም ከሀገር ውስጥ ካሉት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን ጨምሮ በውጪ ካሉት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ ኤፍሬም ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዱስ ባስልዮስን እና እጅግ በዛ ያሉ ሊቃውንት ለእያንድ አንዱ ትንታኔው ማመሳከርያ አድርጎ አንጎራቿል። የትርጓሜ መጻሕፍትን እና ሌሎች ድርሳናትንም ሲያጣቅስ እንመለከተዋለን። እና ደግሞ የሊቃውንቱን አገላለጽ ስንመለከት ወደ ብዙ መደመም እንድንደርስ ያደርገናል። ምን አልባት መጸሐፉን ካደመቁት ነገሮች መካከል አንዱ ብዙ ጊዜ ያልሰማናቸው የሊቃውንተ ንግግሮችና እይታዎች አንደኞቹ ናቸው።

፮:-አንባብያንን ማያደክም የአጻጻፍ ስልት
184 viewsMoges abreham, 13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 22:16:08 ማን ምን ይለየኛል?

ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየኝ ምንድ ነው? መጠማት ነው? ወይስ መቸገር?የቤቴ መጉደል ነው ወይስ መታረዝ ? ሰሎሞን ውዴ ብሎ ከጠራው ከጌታዬ ከክርስቶ ምን ይለየኛል? ውዴን ካገኛችሁት ከፍቅር የተነሳ መታመሜን ንገሩት ብሎ የተናገረው ጠቢብ ምን ይደንቅ? በደሙ ፍቅሩን ከገለጠለኝ ከክርስቶስ ፍቅር ዓለም አትለየኝም? እየተራብኩኝ ስለ እኔ የተራበውን ክርስቶስን አስባለው። እየተጠማው ተጠማው ብሎ ስለ እኔ የተጠማውን እሱን አስባለው። ለማን ሆነና መገላታቱ? ለማን ሆነና መሰቀሉ? ለማን ሆነና ስድብ መታገሱ? እኔ ግን ፍቅሩ ከዓለም ብልጭልጭ ሁሉ በልጦብኛል። ፍቅሩ ዓለሙን ከነኑሮዎ አስረስቶኛል። ደም ግባት እስክናጣለት ድረስ መከራ ከተቀበለ ከክርስቶስ የሚያርቀኝ የትኛው ችግር ነው? የትኛው ዘለፉ ነው? እኔ ግን ዮሐንስን መሆን ተመኘው እድሜ ዘመኑን የክርስቶስን ፍቅር እያሰበ ያለቀሰውን። እኔ ግን ሐዋርያትን መሆን ተመኘው እብድ ለተባሉበት የክርስቶስ ፍቅር የኖሩትን። ሰው ምን ያደርገኛል? ድኅነት ነፍሴን ምን ይጎዳታል? ክርስቶስ ግን የነፍስ መድኃኒት ነው። ክርስቶስን ማታብ ነፍስ ፍዳዋ ምን ይሆን? የክርስቶስን መከራ አስባ ማታለቅስ አይኔ ግን መጨረሻው ምን ይሆን? ነፍሴ ሆይ መድኃኒትሽን አትርሺ ጌታሽን ውደጂ እልሻለው።

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
273 viewsMoges abreham, 19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 21:16:42 እግዚአብሔር እንዳንታበይ አንድ እንከን ያሳድርበናል። እጅግ ሀብታም ብንሆን አምላኬ ሆይ ማረኝ የሚያስብል በሽታ ይኖርብናል። እጅግ ጤነኛ ብንሆን የእለት እንጀራዬን አትንሳኝ የሚያስብል ድኅነት ይኖርብናል። እጅግ እውቀት ቢኖረን ሰዎችን ማሳመን የሚችል ጥበብ ላይኖረን ይችላል። እጅግ ውበት ቢኖረን ከሰው ጋር ማያስኖረ ጠባይ ያድርብናል። እጅግ ጥሩ ጠባይ ቢኖረንም ሰዎች እንዲያዩን የሚያደርግ እውቀት ላይኖረን ይችላል እጅግ ዝና ቢኖረን እንቅልፍ የሚነሳ ጭንቀት እና ሰላም ማጣት ይኖርብናል። ሁል ጊዜ ሙሉ መሆን አይቻልም። ሁልጊዜ እርሱን እንድናስብ የሚያደርግ አንድ ጉድለት ይኖርብናል። ባገኘነው እንዳንታበይ የማይሰጡን ብዙ ጸጋዎች አሉ። ፍጹም የሚባል ሰው ማን ነው?በሁሉም የትምህርት አይነቶች ላይ አንቱ የተባለ ማነው? እስከ ሞት ድረስ የሚዘልቅ ደስታ ያለው ማን ነው? እኛ በተከበርንበት ቦታ ሌላ የሚከበር ሰው ይነሳል እኛ አዋቂ በተባልንበት ቦታ ከእኛ የተሻለ አዋቂ ይነሳል። ጎዶሎ ነገሮቻችን እግዚአብሔርን እንድናስታውስ ይረዱናል።

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
16/10/2014
272 viewsMoges abreham, edited  18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 16:34:17 ከመሣርያ ጥበብ ይሻላል

ጠቢቡን አለማድነቅ ይቻል ይሆን? ይህ ጠቢብ ሰለሞን ነው። እጅግ አስደሳች ቃላቶችን ይጠቀማል ውብ አገላለጾቹ ልብን ይጎትታሉ ። እናም አንድ አንድ ቃላቶቹን እንድናስብ ያደርገናል። ወቅቱን የሚወክል አንዱን ምክሩን ብቻ እንይ ጠቢቡ “ከጦር መሣሪያዎች ይልቅ ጥበብ ትሻላለች፤ ።”(መክብብ 9፥18)። ይላል ይህም ዘመናትን የሚሻገር እውነት ነው።መሣርያ የሚገነባው አእምሮ እንዴት ያለ አእምሮ ነው? በመሣርያ የሚገነባ ቤት መሠረቱ ምን ይሆን? በመሣርያ የተጀመረ ጸብ ማለቅያው ምንድን ነው? ጥበብ መሣርያን አትሻም እውቀትን እንጂ። ጥበብ የተረጋጋች ከተማን እንጂ ሰላም ያጣች ከተማ ላይ አታድርም። ከመሣርያ ጥበብ ከጦርነት ደግሞ እውቀት እንደሚሻለ ለምን ዘነጋን። ሰሎሞን ጥበብን ስለቀመሰ መሣርያንና ጦሮችን ሁሉ ጠላ እውቀትን ግን አብልጦ ወደደ። ጠቢቡ ሀገሩ ሰላም ሆኖለት አስተዳድሯል ምሥጢሩ ከጦር ይልቅ በጥበብ ስለመራችው ነበር። ጥበብ የጎደለው መሪ መፍትሔው ጦር እና መሣርያ መሆኑ ነው።ፍርድ የሚቀናለት ጥበበኛ መሆን በእውነት መመረጥ ነው። የኛ ትውልድ ጥበብ ጉድሎት ተመለከትን።ጦር እና ጦርነት ለምን መፍትሄ አደረገ። ጠቢብ ሰዎች የበዙበት ሀገር ውስጥ ሰላም ስቆ ይታያል በዛች ከተማ እውቀት ብቻ አሸናፊ ይሆናል። ጦር ጥላቻ የወለደው ነው እንጂ ከጥበብ የተቀዳ አይደለም።


ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
10/9/2014
348 viewsMoges abreham, edited  13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:35:56 ስለ መጻሕፍት ንባብ ከማኅበረ ቅዱሳን tv ጋር ያደረኩት ቆይታ



287 viewsMoges abreham, 13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 12:37:09 እንዴት ያለ ዝምታ ነው


በአባቶች ታሪክ ውስጥ ለትእግስት ምሳሌ ሚሆንን ማን ነው? ምን አልባት ብዙ የተፈተነው ኢዮብ ሊሆን ይችላል። ለሚወዳት ለራሄል 14 ዓመት የተገዘው ያዕቆብን ልታነሱ ትችላላችሁ? አኗኗራቸው የማይመች የነበረ ሕዝበ እስራኤላውያንን ሲመራ የነበረው ሙሴ የሚልም አይጠፉም። ከሁሉም የሚያስገርመው ግን "የክርስቶስ ትእግስት" ነው። ተመልከቱ በፈጠራቸው እጆች በጥፊ ሲመታ ዝም አለ? በምራቅ አይን ያበራ ምራቅ ሲተፉበት ዝም አለ። ከሰማይ መና ያወረደ አምላክ ሆኖ ሐሞት ሲያጠጡት ዝም አለ። እርሱ እኮ ሰማያትን የዘረጋ ምድርን የፈጠረ አምላክ ነው እርሱ እኮ ሰማይ ዙፉኑ የሆነለት ምድር መረገጫው የሆነችለት ነው። መላእክት ሊቀርቦት እንኳን አይችሉም። በሰዎች ግን በመሬት ተጎተት በመሰቀል ዋለ። ያንን ጲላጦስ ምን ያስገረመው መሰለህ የክርስቶስ ዝምታ ነው ይህን ሁሉ ሲሉህ ዝም ነው ምትለውን አለው። እንዴት ያለ ትእግስት ነው ከአንደበቱም አንዲት የርግማን ቃል አልወጣም። ባሪያ ንጉሥ ላይ ምራቅ ቢተፋ ምን ይገጥመዋል? ሎሌ ጌታውን ቢሳደብ ምን ይጠብቀዋል? የሰማይና የምድር ንጉሥ ግን የፈጠራቸውን ታገሳቸው። ጌታዬ ትእግስትህን ምን አንደበት ይናገረዋል?

"ኦ ትእግስት ዘኢከሠተ በአፋሁ"

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
5/9/2014
397 viewsMoges abreham, edited  09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 21:17:39 የሶምሶን "ሴት"...


ሶምሶን የተባለ ኃያል ሰው በምን ምክንያት ወደቀ? የአንበሳ ያክል ጥንካሬ የነበረው ያ ታላቁ ሶምሶን ኃይሉ እንዴት ተወሰደበት? በአንዲት ሴት ምክንያት አይደለምን? የሶምሶን ሴት ደሊላ ከእግዚአብሔር ጋር ይኖረ የነበረውን ኃያል ሰው በወጥመዷ በጣለችው ጊዜ ሶምሶን አይኑ ታወረ በፍቅሯ በመያዙ አላስተዋለም። ይህቺ ሴት ግን ወዳጅ መስላ ከፈጣሪ የተሰጠውን ኃይል አስወሰደችበት። የሶምሶን ሴት እጅግ ነውረ የነበረባት ነበረች። ከነውረኛ ሴት ጋር ወዳጅነት የጀመረ ሰው ፍጻሚው እንዴት የከፉ ይሆን? በመልኳና በሰውነቷ ታውሮ ሞትን መምረጥ ምን ያህል ጠማማነት ይሆን። እግዚአብሔርን ምትፈራ ሴት ግን ለወዳጇ ዘውድ ናት። እንደ ሶምሶን ሴት ያሉትን መጠንቀቅ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ቆይታ ያረዝምልናል። የደሊላ ልጆች መነኮሳትን እንኳን ከማሳት ወደኋላ አይሉም። እነርሱ የተመረጡትን ጭምር ያስታሉ። በንግግራቸውና በአለባበሳቸው ወደ ዝሙት መንገድ ለመውሰድ ይደክማሉ። አንተ የመራጥካት ሴት ደሊላ ከሆነች አስተውል። ኃይልህን ጉልበትህን ልታሳጣህ ትችላለችና አስተውል። እግዘብሔርን የምታሰተው ሴት ላንት አትሆንህምና አስተውል። እንግዲህ ከእግዚአብሔር ይልቅ የደሊላ መልክና ሰውነት የማረከህ እንደሆነ ቆም ብለህ አስብ። ያ ምስኪን ሶምሶን በደሊላ ምክንያት በፍልስጤማውያን እጅ ወደቅ እስከሞትም ደረስ። ከእግዚአብሔር ሰው ይልቅ የፍልሰጤማውያንን ገንዘብ ወዳ ሶምሶንን ምን እንዳደረገችው ተመልከት ኃይሉ በጸጉር ላይ እንደሆነ አምኖ ቢነግራት በጉልበቷ ላይ አስተኝታ ጸጉሩን ገመደችው እግዚአብሔርም ተለየው። ወንድ ሆይ ከጋለሞታ ሴት ጋር ሚስጥርህን አትጋራ ሽቶዋ አይሳብህ ገንዘብን አብልጣ ከምትወድ ሴት ጋር አትውደቅ። መልኳና ሰውነቷ ሳይሆን እግዚአብሔርን መፈራቱ ብቻ በቂህ ነውና አስተውል።


ዲ/ን ምገስ አብረሃም
4/9/2014
268 viewsMoges abreham, edited  18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 20:56:08
የሰው ልጆችን ታሪክ የቀየሩ ሁለት ድንቅ ልደቶች አሉ። እነዚህ ልደቶች ለሰው ልጆች መዳን መጀመርያ ናቸው። አንደኛው በከብቶች በረት የተፈጸመው የጌታችን ልደት ሲሆን ሁለተኛው ልደት ደግሞ በሊባኖስ ተራራ ላይ የተመለከትነው የእመቤታችን ልደት ነው። የአምላክ እናት ለመሆን የተመረጠችው እመቤታችን ከቤት ውጪ ውርጭ በበዛበት በሊባኖስ ተራራ ተወለደች የሰማይና የምድር ንጉሥ የሆነ ጌታችን ደግሞ እጅግ በተናቀ ስፍራ በበረት ተወለደ። የንጉሥ እናቱና ንጉሥ እንዴት ባለ ስፍራ እንደተወለዱ ተመለከት። እንዲ ያለውን ትህትና የሚገልጽ ምን አይነት ቃል ይኖራል። መላእክት እጅግ የተደሰቱባቸው ልደቶች እነኚህ ናቸው። የመላእክትና የሰው ልጆች ኅብረት ዳግመኛ እንደ አዲስ እንዲወጠን ምክንያት የሆኑ በምድራችን የተፈጸሙ ድንቅ ልደቶች ናቸው። በእናት እና በልጁ ልደት ላይ እጅግ የተከበሩ የምድረ ነገሥታት አልተገኙም የቤተመቅደስ ካህናትና በጊዜው የነበሩ እውቅ ሰዎቹ አልነበሩም። በሁለቱም ስፍራዎች ግን ታላቅ ደስታ ነበር። ምድር ላይ ባልታየ ሁኔታ በጌታችን እና በእመቤታችን ጊዜ ዓለም ብርሃንን ተሞልታ ነበር።

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም የልደት ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
604 viewsMoges abreham, 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 12:32:50 የሚበላ አላችሁን


በመስቀል ላይ ተጠማው ሲል የሰማነው ጌታችን ከትንሣኤ በኋላ በሦስተኛ ሳምንት ደግሞ ዳግመኛ ለሐዋርያቱ የሚበላ አላችሁን አላቸው። እነ ጴጥሮስ ጥብርያዶስ ምትባል ባሕር ላይ እያጠመዱ ሳለ ነበር ተገልጾ እንዲህ ብሎ የጠየቃቸው። አይደለም ሰውን ይቅርና እንስሳትን የሚመግብ ጌታ "የሚበላ አላችሁን" ብሎ መጠየቁ ምሥጢሩ ምን ይሆን? ባሕር አሳን እንድታወጣ ያደረገ ጌታ ተርቦ ይሆን እንዲህ ማለቱ? ምሥጢሩ ይህ ነው ጌታችን ምግቡ የሰው ልጆች ሥራ መጠጡ የሰው ልጆች የንሰሐ እንባ ነው። ሙሴ በአንድ ወቅት ምን ትበላለህ ብሎ በመደነቅ ጠይቆት ነበር። ሙሴ ጌታን ትበላለህን? አለው አዎን ትጠጣለህን? አለው አዎን አለው። ምን ትበላለህ ወይስ ምንስ ትጠጣለህ ብሎ ቢጠይቀው ሰው ኃጢአት ሠርቶ ንሰሐ ገብቶ ሲያለቅስ ያንን እመገባለሁ ብሎታል። ተመልከቱ የእግዚአብሔር ምግብና መጠጥ የእኛ መልካም ሥራ እና የንሰሐ እንባ ነው። ለጌታ የሚሆን ምግብ ምን አለን? እሱን የሚያስደስት መጠጥ ከወዴት ይገኛል? የምድር ነገስታት እጅግ የጣፈጡ ነገሮች ተመግበው አልፈዋል።የሰማይና የምድር ንጉሥ ፊት የሚቀርብ ምግብ እንዴት ያለ ነው? የዚህ መልስ ብዙ አያመራምርም ጌታን ደስ የሚያሰኝ ሥራ መሥራት ኃጢአትን አስቦ ማዘን ለእርሱ መልካም ምግብ ነው። የሚበላ አላችሁን ብሎ የጠየቀን እለት ለጌታ ምን ይሆን ምናቀርበው? የትኛውን ሥራችንን ይሆን ምናሳየው?


ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
28/8/2014
387 viewsMoges abreham, 09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ