2024-05-18 11:46:25
በቲክቶክ ለታማሚዋ የተሰበሰበውን ብር ይዞ የተሰወረው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ።
#FastMereja
ምህረት ሀደራ የተባለች አህታችን ያልፍልኛል ቤተሰቤንም ካሉበት ችግር አግዛለው ብላ በህገ ወጥ መንገድ ወደ አረብ ሀገር ብትሄድም ነገሮች እዳሰበችው ሳይሆን በተቃራኒው ጭኗ ላይ ከፍተኛ እባጭ በመውጣቱና ወደ ካንሰር በመቀየሩ ችግር ውስጥ ትገባለች።
ህጋዊ አለመሆኗ ደግሞ በዛ ሀገር መታከም አለመቻሏ ችግሩን ያበዛባታል። ይህን በሽታ ይዛ ለሁለት አመት ከቆየች በኋላ ካቅሟ በላይ ሲሆንባት ጉዳዩን ወደ ማህበራዊ ሚዲያ ይዘው በመምጣት በመላው አለም ያሉ ኢትዮጲያዊያን በማገዝ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በማዋጣት እሷም ወደ ሀገር ገብታ እድትታከም እሷን በኤርፖርት በመላክ የተሰበሰበውን ብር በአቶ ተስፋዬ ስዩም በሚባል ተጠርጣሪ በኩል እንዲደርሳት ቢላክም አቶ ተስፋዬ ስዩም ገንዘቡ አካውንቱ እደገባለት እራሱን ለመሰወር ቢሞክርም የንፋስ ስልክ ላፍቶ ፖሊስ መምሪያ ከቅን ልቦች በደረሰው አቤቱታ እና ጥቆማ መሰረት ባደረገው የነቃ ክትትል በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር መዋሉን ቅን ልቦች ለፋስት መረጃ ባደረሰው መልዕክት ያሳያል።
ማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባህልና እሴቶቻችንን የምናሳድግበት ለተቸገረ የምንረዳዳበት እንጂ ከነበርንበት የዃሊት የምንሸራተትበት መሆን የለበትም ሲሉ ቅን ልቦች መልዕክት አስተላልፏል ግለሰቡ በአሁን ሰአት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ፖሊስ መምሪያ ይገኛል።
****
https://t.me/danny4677
10.6K views08:46