Get Mystery Box with random crypto!

አንድ ሰው በመንገዱ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ ነገር አየ። ቀረብ ብሎ ማንበብ ጀመረ... 'ትናንት | Emir consult

አንድ ሰው በመንገዱ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ ነገር አየ። ቀረብ ብሎ ማንበብ ጀመረ...

"ትናንት ሃምሳ ብር እዚህ መንገድ ላይ ጠፍቶብኛል። እኔ አይኖቼ ስለደከሙ ላገኘው አልቻልኩም። ብሬን ያገኛቹ ከሆነ እባካችሁ እዚህ ባለው አድራሻዬ አምጡልኝ!!" ይላል።

ይህን ካነበበ በኋላ ሰውየው 50 ብር በጣም ትንሽ ብር ሆኖ ሳለ አንድ ሰው እንዴት ይህንን ማስታወቂያ ሊለጥፍ ይችላል? ብሎ ራሱን ጠየቀ።
ብሩ ትንሽ ቢሆንም ይህን መልዕክት ላስቀመጠው ሰው በጣም አስፈላጊ መሆን አለበት ብሎ አስቦ በተጠቀሰው አድራሻ መሰረት አንድ ደሳሳ ቤት ደረሰና በሩን አንኳኳ።
በዚህ ጊዜ አንዲት ምስኪን ሴት በሩን ከፍተው ብቅ አሉ።

ትንሽ ካወሩም በኋላ ሴትዮዋ እዚህ ቤት ውስጥ ብቻዋን እንደምትኖር ተረዳ።
ሰውዬውም "እማማ የጠፋቦትን 50 ብር ስላገኘውት ልሰጥዎት ነው የመጣሁት" አላቸው።
ይህን ሲላቸው ሴትዮዋ ማልቀስ ጀመሩ።
"ልጄ እስካሁን ከ70-75 የሚጠጉ ሰዎች 50 ብሩን አጊንተናል እያሉ ቤት እየመጡ ሰተውኛል።እኔ ማንበብ አልችልም፣ ምኖረውም ብቻዬን ነው፣ አይኖቼም ደካማ በመሆናቸው ይህ የተለጠፈው የት እንደሆነም አላውቅም።
ይህንን ሁኔታዬን የተረዳ አንድ ሰው እኔን ለመርዳት ያን ወረቀት ለጥፎት መሆን አለበት። እኔ የጠፋብኝ ብር ስለሌለ አልቀበልም።"አሉ።

ሰውዬው ግን እናትዬውን በማፅናናት ብሩን እንዲቀበሉ ያደርግና ተመልሶ እንደሚመጣ እና እንደሚጎበኛቸው ቃል በመግባት ተሰናበታቸው።

እሳቸው ግን፦ "ልጄ እባክህ የተለጠፈውን ወረቀት ቀደህ ጣልልኝ።እኔ ይህን ማድረግ ስለማልችል ነው የምጠይቅህ።" ብለው ለመኑት።

ሰውዬውም "እሺ እማማ" ብሎ ተሰናበታቸው።
እሺ ቢላቸውም እንዲህ ሲል ግን አሰበ፦ "ከዚህ በፊት ወረቀቱን እንዲቀዱላቸው የመጡትን ሰዎች ሁሉ ጠይቀው ይሆናል ግን ማንም ሰው ሳይቀደው እኔ ለምን እቀደዋለሁ።"
ከዚያው ይቺን ደካማ ሴት ለመርዳት ይህን መንገድ ያሰበው ሰው ምን ያህል ደግ ሊሆን እንደሚችል አስቦ አደነቀም።

       #ፍላጎቱና ተነሳሽነቱ ካለ አንድን ሰው ለመርዳት ብዙ መንገዶች አሉ!! መልካም እንሁን፣ መልካም እናስብ መልካምነት ለራስ ነው።
Emir consult:
በፈጣሪህ ብቻ ተመካ !

እዚህች ምድር ላይ ብዙ የምትወዳቸው ሰዎች ይኖራሉ ነገር ግን አንዳቸውም የፈጣሪን ስራ አይሰሩም እርሱ የሚያደርግልህን ሊያደርጉ አይቻላቸውም !

"በፈጣሪ የማይሆን አንዳች ነገር የለም ሁሌም በእርሱ ተስፋ አድርግ
https://t.me/consult_emir

የእናንተው ምርጥ ጓደኛ!

https://t.me/consult_emir