Get Mystery Box with random crypto!

በዝውውር መስኮቱ 17 ተጨዋቾች ብቻ ዝውውራቸው ጸድቋል #እስካሁን_ፌዴሬሽን_ያወቀው_ዝውውር_የአራ | የቡና ጉዳይ ይመለከተኛል

በዝውውር መስኮቱ 17 ተጨዋቾች ብቻ ዝውውራቸው ጸድቋል

#እስካሁን_ፌዴሬሽን_ያወቀው_ዝውውር_የአራት_ክለቦችን_ብቻ_ነው።

ሀምሌ 1 በይፋ በተከፈተው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ባለፉት ስድስት ቀናት ብቻ ህጋዊ ዝውውር ያደረጉት ተጨዋቾች ከ20 እንደማይበልጡ ተነገረ።
ከክለቦቹ ታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ

#ኢትዮጵያ_ቡና ብሩክ በየነ፣ አብዱልከሪም ወርቁ፣ ጫላ ተሺታ፣ ሀይለሚካኤል አደፍረስ፣ አብዱል ሀፊዝ ቶፊቅና መስፍን ታፈሰን ሲያስፈርም የሮቤል ተ/ሚካኤል ውልን ማራዘሙ ታውቋል። በርካታ ዝውውር እያደረገ ነው የተባለው

#መከላከያ በረከት ደስ፤ ዳግም ተፈራ፣ ምንይሉ ወንድሙና ሳሙኤል ሳሊሶን ሲያስፈርም

#ፋሲል_ከነማ በበኩሉ የበዛብህ መለዮ፣ የሱራፌል ዳኛቸውና የሽመክት ጉግሳን ውል ሲያድስ

#ባህርዳር_ከተማ ፍጹም ጥላሁን፣ ያሬድ ባዬህና ዱሬሳ ሹቢሳን ማስፈረሙ ታውቋል።

ከ16ቱ ክለቦች እስካሁን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ማረጋገጫ ያገኙት #አራት_ክለቦች ብቻ መሆናቸው ታውቋል።

ምንጭ #ሀትሪክ_ስርአት

@bunawuatiawaki
@bunawustiawaki