Get Mystery Box with random crypto!

ንባብ ለወሬ 'ንባብ ለህይወት'፣ 'ንባብ ለዕውቀት'፣ 'ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል'... የሚሉና | ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA

ንባብ ለወሬ

"ንባብ ለህይወት"፣ "ንባብ ለዕውቀት"፣ "ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል"... የሚሉና ሌሎችም ስለ ንባብ የተጠቀሱ ተመሳሳይ አባባሎች አሉ። ማንበብ ግን ለወሬ እንኳ ቢሆን አስፈላጊ ነው። ይህም ከንባብ ጥቅሞች አነስተኛው ደረጃ (minimum of requirement) ነው ማለት ይቻላል። ያነበቡና ሌጣቸውን የሆኑ ሰዎች የሚያነሱት ጨዋታ እንኳ ወዙና ለዛው ለየቅል ነው። የወሬያቸው ጣዕም የእንጨትና የሙዝ ያህል ሆኖ ልዩነቱ በግልፅ ይስተዋላል። ሳሙኤል ቤከር የተባለ ጸሐፊ "ማንበብ የዕውቀት መሠረት ነው። የማያነብ የሚያስበው ያጣል የሚናገረውም ያንሳል" ሲል መናገሩ ምንኛ እውነት ነው..! የማሰላሰል አድማሳችንና ርዕሳችን እንዲሰፋ፣ ንግግራችን ጥልቅ፣ ጥብቅና ማራኪ እንዲሆን ሁነኛው መድኅን ንባብ ነው።

የንባብ ጥም መቁረጫ ምንጮች የሆኑ መጻሕፍት "ንባብ ለህይወት" በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከዛሬ ሐምሌ 28 እስከ ነሐሴ 2 / 2014 ዓ.ም ድረስ በሚዘልቅ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ይቀርባሉ።

በኤግዚብሽኑ የታሪክ፣ የፍልስፍና፣ የረዥምና አጭር ልብ ወለድ፣ የስነ-ግጥም፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካ፣ የታዋቂ ሰዎች ግለ ታሪክና ሌሎችም መጻሕፍት ለእይታና ለሽያጭ ቀርበዋል። በአውደ ርዕዩ በርካታ መጻሕፍት መደብሮችና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ስለሚሳተፉበት ከገበያ የጠፉ የቀድሞ መጻሕፍትና በቅርብ ጊዜ ለሕዝብ የተዋወቁ አዳዲስ መጻሕፍትም ይገኛሉ። በ2012 ዓ.ም እና በያዝነው 2014 ዓ.ም ለሕትመት ያበቃኋቸው "ምልሰት" እንዲሁም "የሳንኮፋ ሰንኮፍ እና ሌሎች" የተሠኙ መጻሕፍቶቼ በኤግዚብሽኑ ይገኛሉ።

አንባቢያን አውደ ርዕዩን ጎብኙ... መጻሕፍትን ግዙ... አንብቡ...!