Get Mystery Box with random crypto!

ቤተ ውዳሴ

የቴሌግራም ቻናል አርማ betetsadkanyeguzomahber — ቤተ ውዳሴ
የቴሌግራም ቻናል አርማ betetsadkanyeguzomahber — ቤተ ውዳሴ
የሰርጥ አድራሻ: @betetsadkanyeguzomahber
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 207
የሰርጥ መግለጫ

🙏 እንኳን በሰላም መጡ🙏
ሰላም የተዋህዶ ልጆች በዚህ የቴሌግራም ገጽ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማ፣ቀኖና እና ትውፊትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮና ትምሕርቶች እንዲሁም ዝማሬዎች ይቀርቡበታል። ክርስቲያናዊ የሆኑ ማህበራዊ ጉዳዮችም ይነሱበታል።በተለይም በተለያዩ ጊዜያት የምናደርጋቸው የየአድባራትና ገዳማት ጉዞዎች ይተዋወቅበታል።

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-17 14:19:19
135 viewsBereket Damene, 11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 14:19:11 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

ሰኔ ፲፩ (11) ቀን።

እንኳን ለኢትዮጵያውያኑ ጻድቃን ነገረ ማርያምን ወደ ግእዝ ቋንቋና አራቱ ወንጌልን ወደ ተለያየ ቋንቋ ለተረጎሙት ለአቡነ መዝሙረ ድንግል ለዕረፍታቸው በዓልና በግብጽ ቤተ ክርስቲያ ጨምር ቅድስና ለተሰጣቸው ለአብረ ገብረ ኢየሱስ ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

+ + +
አቡነ መዝሙረ ድንግል፦ የተባሉት ጻድቅ አገራቸው ጎጃም ነው፤ ታላቅ የቤተ ክርስቲያናችን ባለ ውለታ ናቸው። ጻድቁ በአምስት ሊቃውንት እየተመሩ በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ አራቱን ወንጌላት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎም በግእዝ፣ በአረማይክ፣ በዕብራይስጥና በዐረብኛ ጽፈው በአራት ዓምት ያዘጋጁ ታላቅ አባት ናቸው። ዛሬም በሞጊና ገዳም ይገኛል።

ከዚህም ሌላ ነገረ ማርያምንም በግእዝና በዕብራይስጥ አዘጋጅተው ጽፈውታል። ሌሎችንም በርካታ መጻሕፍት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች እየተረጎሙ ጽፈው ያስቀመጡ ነበር። በጣም ጸሎተኛ፣ ደራሲ፣ ባሕታዊ፣ ጻድቅና መናኝ የሆኑት አቡነ መዝሙረ ድንግል ዐርፈው የተቀበሩት ጣና ክብራን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነው። ከአቡነ መዝሙረ ድንግል እግዚአብሔር አምላክዐ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!።

+ + +
አቡነ ገብረ ኢየሱስ፦ የተባሉት ኢትዮጵያዊ ጻድቅ በአገራችን ብዙ ተአምራትን በማድረግ ወንጌል ሲሰብኩ ከኖሩ በኋላ የግብጽ ገዳማትን ለመሳለም ወደ ግብጽ ወርደው አባ መቃርስ ገዳም ገቡ። ከዚያም ወጥተው በአባ ዮሐንስ ሐፂር ገዳም ገብተው በዚያ ብዙ ጊዜ ተቀመጡ። አቡነ ገብረ ኢየሱስ ታላቅ የሆነ ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባት ስለሆኑ በዚህም ግብጻውያን ይቀኑባቸው ነበር።

ስልሳ ስድስተኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ገብረ ክርስቶስ ባረፉ ጊዜ ኤጲስቆጶሳቱ ተሰብስበው ወደ አባ መቃርስ ገዳም ወደ አስቄጥስ መጥተው ለከበረች ሹመት የሚገባውን እየመረመሩ ሁለት ወር ተቀመጡ። በዚህም ጊዜ በአባ ዮሐንስ ሐፂር ገዳም ለሚኖሩት ለጻድቁ አቡነ ገብረ ኢየሱስ የታዘዘ መልአክ ተገልጦላቸው "ለኤጲስ ቆጶሳቱ ለዚህች ለከበረች ሹመት የሚገባው ስሙ ገአርጊ የሚባል በመካከላችሁ አለና እርሱን ሹሙት አትዘኑ" በላቸው ብሎ ነገራቸው። አቡነ ገብረ ኢየሱስም "ከመካከላችሁ ስሙ ገአርጊ የሚባል ጻድቅ አለና እርሱን ሹሙት" ብለው መልአኩ የነገራቸውን መልእክት ነግረዋቸው አባ ገአርጊን ስልሳ ሰባተኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾመዋቸዋል።

አባ ገአርጊም ስማቸው አባ ቄርሎስ ተብሎ ከተሾሙ በኋላ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ አገልግለዋል። በወቅቱ የነበረው የግብጻውያኑ ንጉሥ በጣም ብዙ ሚስቶች የነበሩት ቢሆንም አቡነ ገብረ ኢየሱስ ሄደው በድፍረት አስተምረውትና ገሥጸውት በአንድ ሚስት ብቻ እንዲጸና አድርገውታል። የጻድቁ አባታችን ገዳላቸው በጣና ይገኛል። ሰኔ11 ቀን ዐርፈው የተቀበሩት ግን በዛው በግብጽ በቊስቋም ገዳም ነው። ግብጻውያን የቅድስና ማዕረግ ሰጥተዋቸው ታቦት ቀርጸውላቸው በዓላቸውን በሚገባ ያከብሩላቸዋል። ከአቡነ ገብረ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳት በዓላት።
132 viewsBereket Damene, 11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 08:41:44
125 viewsBereket Damene, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 08:41:34 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

ሰኔ ፲ 10

እንኳን ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ለሆነበት መላእክትም በሰማያት ደስ ለተሰኙባት ቀን በዓል (በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘጉ አብያተ ክርስቲያናትም እንዲከፈቱ ትዕዛዝ ወጥቷልና)፣ ለቅዱሳን ደናግል ደባሞንና ብስጣሞን ለእናታቸው ለቅድስት ሶፍያ ሰማዕታት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከእነ ቅድስት ሶፍያ ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ከቅድስት ዮና ከቅዱሳን ዋርስኖፋና አውሎጊስ ከመታሰቢያቸው፣ ከሰማዕት ከቅዱስ አቅሊሞስ፣ ከአባ ነአንና ከይስካ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

+ + +
በዚች ዕለት ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ መላእክትም በሰማያት ደስ ተሰኙባት። በዚች ቀን እውነተኛ ምዕመን ከሆነ ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘጉ አብያተ ክርስቲያናትም እንዲከፈቱ ትዕዛዝ ወጥቷልና።

ደስታን የተመላች ያች መልእክት ወደ እስክንድርያ ከተማ እንደ ዛሬዋ ቀን በደረሰች ጊዜ ፈጽሞ ደስ ተሰኙ ወደ ግብጽ አውራጃዎችም ሁሉ ላኳት ምዕመናን ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን ክብር ከፍ ከፍ ማለት ደስ አላቸው የጣዖታት ቤቶችንም ዘጓቸው አብያተ ክርስቲያናትንም ከፈቱአቸው እንደ ዛሬም በዚች ዕለት ሰኔ 10 ቀን በዓል አደረጉ ይኸውም ቈስጠንጢኖስ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመቱ ነበር እለእስክድሮስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ነበር። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታውና ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን።

+ + +
ቅዱሳን ደናግል ደባሞንና ብስጣሞን እናታቸው ቅድስት ሶፍያ፦ እንዲህም ሆነ ስሙ ዋርስኖፍ የሚባል አንድ ሰው ነበረ ኤጲስቆጶስነት ሊሾሙት በወደዱ ጊዜ ሸሽቶ ወደ ናባ አውራጃ እሊህ ደናግል ወዳሉበት ወደ ግሕሙን ደርሶ በዚያ አደረ። በዚያቺም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት "ከዚህ ለምን ትተኛለህ ተነሥተህ ተጋደል ለአንተና ሰማዕት መሆን ለሚሹ ሁሉ አክሊል ተዘጋጅተቀልና አሁንም ተነሥተህ ወደ መኰንኑ ሒድ በፊቱም ቁመህ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመን" አለው። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለቅዱሳን ደናግል ነገራቸው።

ሲነጋም ተነሥተው ከእርሱ ጋራ ወደ መኰንኑ ሔዱ በመኰንኑ ፊት ክብር ይግባውና በጌታችን ታመኑ። መኰንኑም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸውና ወደ ወህኒ ቤት ጨመራቸው ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ከዚያ አውጥቶ ከቅዱስ ዋርስኖፍ ጋራ ወደ ስንሑር ላካቸው እናታቸውም ትከተላቸው ነበር። መኰንኑም "ለአማልክት ዕጣን ዕጠኑ" አላቸው ባልታዘዙለትም ጊዜ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ አጸናቸው ቊስላቸውንም ፈወሰ።

ከዚህም በኋላ መኰኑኑ ከእርሱ ጋራ ወደ አገረ ፃ ይዞአቸው ሔደ። የጣዖታቱ ካህናትም ጣዖታቱን እንደምትረግም ስለ ቅድስት ደባሞን ነገሩት እንዲሁም ባልጀራዋ ዮና የምትባል ሴት እንዳለች ነገሩት እርሱም ኅብራቸው በየራሱ የሆኑ መልካም ልብሶችን እየሠሩ ለምግባቸው ይሸጡ ነበር የተረፋቸውንም ይመጸውቱ ነበር። መኰንኑም የዮናን ዜና ሰምቶ ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጥ ባለሰይፉን ላከው የሰያፊውም ስም አውሎጊስ ነው። ወደርሷም በቀረበ ጊዜ ፊትዋ እንደ መላእክት ፊት ብርሃንን ተመልቶ አየና ፈራ እርሷንም ወደ መኰንኑ እንዲወስዳት እንጂ እንዳይገድላት የእግዚአብሔር ጸጋ አስገነዘበችው ቤተ ሰቦቿም ተሰናባብተዋት ጸንፋ ከሚባል አገር ወጣች ወደ አገረ ፃ ደርሳም መኰንኑን ተገናኘችው ከቅዱስ ወስኖፍና ከባልንጀሮቹ ጋራ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ። ሰያፊው አውሎጊስም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነና ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ እንዲሁም እሊያን ቅዱሳት ደናግልንም ራሳቸውን ቈረጧቸው ገድላቸውንም ፈጽመው የድል አክሊልን ተቀበሉ።

ቅድስት ደባሞንን ግን ጽኑዕ ሥቃይ ያሠቃዩአት ዘንድ በመንኰራኵር ላይ ሰቀሉአት። በዚህ ሥቃይም ውስጥ ለብዙ ቀኖች ኖረች የእግዚአብሔር መልአክም ያጸናት ያስችላትና ቊስሎቿን ይፈውሳት ነበር መኰንኑም ወደ ወህኒ ቤት አስገባት በዚያም ጥቂት ቀን ኖረች ወደ ፍርድ ሸንጎም አስቀርቦ "ለአማልክት ሠዊ"" አላት ባልሰማችውም ጊዜ ራሷን እንዲቆርጡ አዘዘ። ራስዋንም ሊቆርጡ ከከተማ ወደ ውጭ በአወጧት ጊዜ ሴቶች ሁሉ እያለቀሱ ከብበዋት ነበር ራስዋንም በሰይፍ ቆረጥዋት እንዲሁም እናቷንና እኅቷን በሰይፍ ቆረጧቸው በመንግሥተ ሰማያትም የድል አክሊል ተቀበለች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በቅዱሳት ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ይድረስን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 10 ስንክሳር።

+ + +
"ሰላም ለሶፍያ ወለአዋልዲሃ ዲባሞን ወብስጣሞን ዘሳተፋ። ይሰነዓዋ ለስምዕ ምስለ ዋርስኖፋ። እማ ወዮና ዘሀገረ ጸንፋ። እምነ ወዲቅ ኪያየ ይሐቅፋ። ከመ ዕጐሊሃ ተሐቅፍ ዶርሆ በክንፋ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ 10።

+ + +
የዕለቱ ምስባክ፦ "ተፈሣሕነ ወተሐሰይነ በኲሉ መዋዕሊነ። ወተፈሣሕነ ህየንተ መዋዕል ዘአሕመምከነ። ወህየንተ ዓመተ አንተ ርኢናሃ ለእኪት"። መዝ 89፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 7፥25-35፣ 1ኛ ዮሐ 1፥4-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 15፥30-36። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 11፥20-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ የዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
183 viewsBereket Damene, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ