Get Mystery Box with random crypto!

16.09.2018

የቴሌግራም ቻናል አርማ bestsportet — 16.09.2018 1
የቴሌግራም ቻናል አርማ bestsportet — 16.09.2018
የሰርጥ አድራሻ: @bestsportet
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.93K
የሰርጥ መግለጫ

...

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-28 20:04:23
አርጀንቲናዊው የማንቺስተር ዩናይትድ አጥቂ አሌሀንድሮ ጋርናቾ በኦልድትራፎርድ እስከ ሰኔ ወር 2028 የሚያቆየውን የኮንትራት ውል ማራዘሚያ ተፈራርሟል

የክለቡ አካዳሚ ውጤት የሆነው የ18 አመቱ ተጫዋች የዋናውን ቡድን ከተቀላቀለ በኋላ በአጠቃላይ 31 ጨዋታዎችን ማድረግ ችሏል።

ተስፈኛው ወጣት ባሳለፍነው ወር ያጋጠመውን የቁርጭምጭሚት ጉዳት ተከትሎ ከሜዳ ርቆ እንደሚገኝ ይታወቃል።

ተጫዋቹ ከጉዳቱ ማገገሙን እና በቅርቡ ወደ ሜዳ እንደሚመለስ ሆላንዳዊው አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ተናግረዋል።

Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
415 viewsYishak Belay, edited  17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 19:50:07
#live

የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ21ኛ ሳምንት ጨዋታ

ቀን:- 20/08/2015

ስታዲየም:- ,Adama Since and Technology University ,Stadium



90'+4'#ተጠናቀቀ

ጨዋታ
                          
    ባህርዳር ከተማ ኢትዮጵያ መድህን
    6' ሀብታሙ           23' ፒተር
     80' አባስ              51'ሀቢብ ከማል
    
                    
                
                Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...


ፎቶ ክሬዲት: የሊግ ካምፓኒ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ
390 viewsYishak Belay, edited  16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 20:47:59 በፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫውን ማረፊያ የወሰኑ የመሪዎቹ ክለቦች የእርስ  በእርስ ግጥሚያዎች

አርሰናል በፕሪሚየር ሊጉ ነገ ምሽት ወደ ኢትሀድ አቅንቶ ማንቺስተር ሲቲን የሚገጥምበት ጨዋታ የሊጉ ክብር ማረፊያን የሚጠቁም እንደሚሆን በሰፊው እየተነገረ ይገኛል።

ሲቲ ከመሪው አርሰናል አምስት ነጥቦች አንሶ ሁለተኛ ስፍራ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ከሰሜን ለንደኑ ክለብ አንጻር ግን ሁለት ቀሪ መርሀ ግብሮች ይቀሩታል።ከዚህ ቀደም በሁለት ክለቦች መካከል ከፍተኛ ፉክክር ተደርጎ በእርስ በእርስ ግንኙነታቸው የሊጉ ማረፊያ የተወሰኑ አምስት አይረሴ የሊጉ ጨዋታዎችን ከዚህ በታች እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል።

ኒውካስትል ዩናይትድ  ከ ማንቺስተር ዩናይትድ 1995-96

የኬቨን ኪገን ቡድን በሴንት ጀምስ ፓርክ ማንቺስተር ዩናይትድን ያስተናገደበት ግጥሚያ ነበር።

ማክፓይሶቹ ድል የሚቀናቸው ከሆነ የሊጉን መሪነት ከተከታያቸው በእጅጉ በማስፋት የዋንጫ ተስፋቸውን በእጅጉ ማለምለም ይችሉ ነበር።

የቲንሳይዱ ክለብ ከጨዋታው በፊት ከዩናይትድ በአራት ነጥቦችም በልጦ ተቀምጧል።

በዚያ የውድድር ዘመን በሙሉ የኪገን ቡድን በሜዳው ምንም አይነት ሽንፈት አላስተናገደም።

በጨዋታው ዴንማርካዊው ግብ ጠባቂ ፒተር ሽማይክል  አስደናቂ ብቃቱን ባሳየበት ጨዋታ የሰር አሌክስ ፌርጉሰን ቡድን በኤሪክ ካንቶና ብቸኛ የሁለተኛ አጋማሽ ጎል ማሸነፍ ቻለ።

ዩናይትድ የነጥብ ልዩነቱን በማጥበብ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ የሊጉን ክብር በአራት የውድድር ዘመናት ለሶስተኛ ጊዜ ማሳካት ቻለ።

በዚያ የውድድር ዘመን ፌርጊ በኪገን ላይ የተጫወቱት የአእምሮ ጨዋታም ሁልጊዜም የሚታወስ ነው።

ማንቺስተር ዩናይትድ 0-1 አርሰናል 1997-98

አርሰናል በመጋቢት ወር  ወደ ኦልድትራፎርድ ያቀናው ከመሪው የፌርጉሰን ቡድን በዘጠኝ ነጥቦች አንሶ ነው።

ሶስት ቀሪ ጨዋታዎች ግን ይቀሩት ነበር።

ማርክ ኦቨርማርስ መድፈኞቹ ጣፋጩን ሶስት ነጥብ እንዲያገኙ ያገዘች የማሸነፊያ ጎል ከመረብ አገናኘ።

ፌርጉሰን ከጨዋታው በኋላ ተቀናቃኛቸው ቀሪ ሶስት ጨዋታዎቹን ቢያሸንፍ ከእነሱ በላይ እንደሚሆኑ እንደሚያውቁ ነገር ግን ያንን ማድረግ እንደማይችሉ እና ነጥቦችን እንደሚጥሉ ተናገሩ። ስኮትላንዳዊው ግን ንግግራቸው ስህተት እንደሆነ በስተኋላ ታየ።

የቬንገር ቡድን አጠቃላይ የቀሩትን ተስተካካይ ጨዋታዎች ጨምሮ ስምንቱን በማሸነፍ የሊጉን ክብር አሳካ።

ቼልሲ 2-1 ማቺስተር ዩናይትድ 2007-08

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የተደረገው በፈረንጆቹ ሚያዝያ ወር 2008 ነው።

ዩናይትድ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ያቀናው በመጨረሻዎቹ  ሳምንታት ከነበሩ ሶስት ጨዋታዎች በፊት ነው።

ሁለቱን ክለቦች የለያቸው ደግሞ ሶስት ነጥብ ብቻ ነው።ሰማያዊዮቹ በማይክል ባላክ ጎሎች ታግዘው ሁለት ለአንድ ማሸነፍ ቻሉ።

ዩናይትድ ከዚያ ጨዋታ ሽንፈት አገግሞ ግን በውድድር ዘመኑ መጨረሻ በሁለት ነጥቦች ብልጫ የሊጉን ዋንጫ አነሳ።

ማንቺስተር ዩናይትድ 1-2 ቼልሲ 2009-10

ቼልሲ ወደ ኦልድትራፎርድ ያቀናው በፈረንጆቹ ሚያዝያ 2010 ነው።

ቼልሲ ከፌርጉሰን ቡድን በአንድ ነጥብ ብቻ አንሶ ተቀምጦም ነበር።

በአሽሊ ኮል እና ዲዲዬ ድሮግባ አወዛጋቢ የጨዋታ ውጭ ጎል ሰማያዊዮቹ ሁለት ለአንድ ማሸነፍ ቻሉ። 

ቼልሲ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ቀን ዊጋንን ስምንት ለዜሮ በማሸነፍ የሊጉን ክብር ማሳካት ቻለ።

ማንቺስተር ሲቲ 1-0 ማንቺስተር ዩናይትድ 2011-12

ዩናይትድ ወደ ኢትሀድ ያመራው ከጎረቤት ክለቡ በሶስት ነጥቦች ብልጫ ይዞ ነው።

የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ ደግሞ የሚቀረው የሶስት ጨዋታ እድሜ ብቻ ነው።

አቻ መውጣት የፌርጉሰንን ቡድን ትርፋማ የሚያደርግ ነበር ።

ሲቲ በቪንሰንት ኮምፓኒ የግንባር ኳስ ጎል አንድ ለዜሮ ማሸነፍ ቻለ።

በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ቀን በአይረሴው ጨዋታ የሮቤርቶ ማንቺኒ ቡድን በማትዘነጋው የሰርጂዮ አጉዊሮ የጭማሪ ሰአት ጎል ኩዊንስ ፓርክ ሬንጀርስን ሶስት ለሁለት በማሸነፍ ከአርባ አራት አመታት በኋላ የሊጉን ዋንጫ አነሳ።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
614 viewsYishak Belay, edited  17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 20:44:32
577 viewsYishak Belay, 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 10:22:29
የቀድሞ የአርሰናል ተከላካይ ኮትዲቫሯዊው ኮሎ ቱሬ አሁን ካለው የመድፈኞቹ  ቡድን ውስጥ እንግሊዛዊው ወጣት ቡካዮ ሳካ በ2003-04 የአርሰን ቬንገር "invincibles" ስብስብ ውስጥ የመጫወት አቅም ያለው ነው ሲል ተናግሯል

ቱሬ በመድፈኞቹ ቤት በነበረው ቆይታ ለሁለት ጊዜያት ያህል የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ማንሳት መቻሉ የሚታወስ ነው።በ2011-12 የውድድር ዘመን ደግሞ ለማንቺስተር ሲቲ ተጫውቶ አሳልፏል።

ቱሬ ነገ ምሽት በሁለቱ የቀድሞ ክለቦቹ መካከል በሚደረገው ወሳኝ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ የፔፕ ጋርዲዮላ ቡድን የተሻለ የማሸነፍ እድል ይኖረዋል የሚል እምነት እንዳለውም ጨምሮ አስታውቋል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
815 viewsYishak Belay, edited  07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 08:53:24 ማንቺስተር ሲቲ ከ አርሰናል
    ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ
       ረቡዕ ምሽት 4:00
          በኢትሀድ ስታዲየም

ካታሎናዊው አሰልጣኝ የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ  ማረፊያ በሚወሰንበት ወሳኝ ወቅት ላይ አብዛኛዎቹ ተጫዋቾቹ ከጉዳት ነጻ ሆነውለት ይገኛሉ።

ሲትዝኖቹ በውድድር ዘመኑ ለሶስትዮሽ ዋንጫ ክብር እየተፋለሙም ነው።

በኤፍኤካፕ ግማሽ ፍጻሜ ሲትዝኖቹ ሼፍልድ ዩናይትድን ሶስት ለዜሮ በረቱበት ግጥሚያ ላይ በጡንቻ መሳሳብ ጉዳት ምክንያት መሰለፍ ያልቻለው ሆላንዳዊ ተከላካይ ናታን አኬ ግን በነገው ጨዋታ ላይ የመሰለፉ ጉዳይ አጠራጣሪ ነው ተብሏል።

በመድፈኞቹ ቤት ግን በርከት ያሉ የጉዳት ዜናዎች አሉ። ፈረንሳዊው ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ በጉዳት ለነገው ጨዋታም እንደማይደርስ ተረጋግጧል።

ታኪዬሮ  ቶሚያሱ እና ሞሀመድ ኤልኔኒ አስቀድሞ ከውድድር ዘመኑ ውጭ የሚያደርግ ጉዳት ያስተናገዱ ተጫዋቾች ናቸው።

ቁጥሮች

ሲቲ በሁሉም ውድድሮች በሜዳው ያደረጋቸውን የመጨረሻ ስድስት ጨዋታዎች በሙሉ ማሸነፍ ችሏል።የጋርዲዮላ ቡድን ከመድፈኞቹ ጋር በሜዳው ባደረገው ያለፉት የሊግ ጨዋታዎች 17-3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። አርሰናል ከ2015 የጥር ወር አንስቶ ሲቲን በኢትሀድ በሊጉ አሸንፎት አያውቅም።

አርሰናል ከሲቲ ጋር ባደረገው አስራ አንድ የመጨረሻ የሊግ ጨዋታዎችም ሽንፈት አስተናግዷል።በሊጉ ታሪክም ከየትኛውም ክለቦች እርስ በእርስ ግንኙነት ከፍተኛው ነው።ቡካዮ ሳካ ከሲቲ ጋር በተደረጉ የመጨረሻ ሁለት የኤምሬትስ የሊግ ጨዋታዎች ኳስ እና መረብን ማገናኘት ችሏል።

በአንድ የውድድር ዘመን በደርሶ መልስ ጨዋታ ሲቲ ላይ ጎል ማስቆጠር የቻለው የመጨረሻ ተጫዋች ግን ቲዮ ዋልኮት በ2016-17 የውድድር ዘመን ነው።

ሲቲ በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው የመጨረሻ አስራ አንድ ጨዋታዎች ማሸነፍ ችሏል።የአርሰናል ወጣት ቡድን በሊጉ የመጨረሻ ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች ነጥብ መጣሉ ከ2004 በኋላ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት ትልቅ ተስፋው አጣብቂኝ ውስጥ እንዲገባ አድርጓል።

አርሰናል በያዝነው የውድድር ዘመን ከሜዳው ውጭ በሊጉ ባደረጋቸው የመጨረሻ አስራ ስድስት ጨዋታዎች በአስራ አምስቱ ጎል ማስቆጠር ችሏል። የሊጉን ማረፊያ ይወስናል ተብሎ የሚጠበቀው ፍልሚያ እጅግ አጓጊ ነው።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
805 viewsYishak Belay, edited  05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 08:52:22
726 viewsYishak Belay, 05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:06:46
አንቼሎቲ ካሪም ቤንዜማ እና ኤድዋርዶ ካማቪንጋ ከስብስቡ ውጭ መሆናቸውን አስታውቀዋል

የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ካርሎ አንቼሎቲ ነገ ምሽት ቡድናቸው ከሜዳው ውጭ በላ ሊጋው ከጂሮና ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ካሪም ቤንዜማ እና ኤድዋርዶ ካማቪንጋ ከስብስቡ ውጭ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ጣልያናዊው ሁለቱ ተጫዋቾች በቀጣዩ ቅዳሜ በሳንቲያጎ በርናባው ከአልሜሪያ ጋር በሚኖራቸው ጨዋታ ላይ ግን ወደ ሜዳ ይመለሳሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ሎስብላንኮዎቹ በቀጣይ በኮፓ ዴላሬ ፍጻሜ ከኦሳሱና እና በሻምፒየንስ ሊጉ ግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታ ከፔፕ ጋርዲዮላው ማንቺስተር ሲቲ ጋር ወሳኝ መርሀ ግብሮች እንደሚጠብቃቸውም ይታወቃል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
858 viewsYishak Belay, edited  18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:06:25
ኮቫቺች ቼልሲን እንደ ቤቱ እንደሚያየው እና በቆይታውም ደስተኛ መሆኑን አስታውቋል

በማንቺስተር ሲቲ እና ባየር ሙኒክ የዝውውር ራዳር ውስጥ የገባው ክሮሺያዊ አማካይ ማቲዮ ኮቫቺች የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ እንደ ቤቱ እንደሚያየው እና በቆይታውም ደስተኛ መሆኑን አስታውቋል።

ኮቫቺች በስታምፎርድ ብሪጅ ያለው የኮንትራት ውል ቆይታ ሊጠናቀቅ የ12 ወራት እድሜ ብቻ ቀርቶታል።

በቅርቡ የቀረበለትን ተጫማሪ የኮንትራት ውል ቆይታ ማራዘሚያ አለመቀበሉን ተከትሎ ከሰማያዊዮቹ ጋር ለመለያየት መዘጋጀቱ ሲዘገብ እንደነበር ይታወሳል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
712 viewsYishak Belay, edited  18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 20:57:42
የቶተንሃም ጊዜያዊ አሠልጣኝ ከአስከፊው ሽንፈት በኃላ ከሀላፊነቱ መልቀቁን ክለቡ አስታውቋል

የቶትንሀም ሆትስፐሩ ጊዜያዊ አሰልጣኝ ክርስትያን ስቴሊኒ የሰሜን ለንደኑ ክለብ ትላንት ማምሻውን ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ አቅንቶ የስድስት ለአንድ ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ ከሀላፊነቱ መልቀቁን ክለቡ አስታውቋል።

ጣልያናዊው የአንቶኒዮ ኮንቴን መልቀቅ ተከትሎ እስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ ቡድኑን በጊዜያዊነት እንዲመራ መሾሙ የሚታወስ ነው።

በቀጣይ ሪያን ማሰን ስፐርስ በሚቀሩት ስድስት የፕሪሚየር ሊግ መርሀ ግብሮች በሀላፊነት ቡድኑን እንደሚመራ ተገልጿል።

ስቴሊኒ ስፐርስን በአራት የሊግ ጨዋታዎች በዋና አሰልጣኝነት መምራት ችሎም ነበር።

Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
676 viewsYishak Belay, edited  17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ