Get Mystery Box with random crypto!

ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኡራጓይ የአለም  ከ20 አመት በታች እግር ኳስ ዋንጫ አሸናፊ  ሆናለች በ | 16.09.2018

ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኡራጓይ የአለም  ከ20 አመት በታች እግር ኳስ ዋንጫ አሸናፊ  ሆናለች

በአርጀንቲና አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየዉ የ2023 ከ20 አመት በታች የአለም እግር ኳስ  ዋንጫ ዉድድር  ሲጠናቀቅ ኡራጓይ ጣሊያንን 1ለ0 በመርታት በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ20 አመት በታች የአለም እግር ኳስ  ዋንጫ አሸናፊ መሆን ችላለች።

ሉቺያኖ ሮድሪጌዝ በ86ኛው ደቂቃ በግንባሩ በመግጨት ያስቆጠራት  ብቸኛ  ጎል ኡራጓይን ሻምፒዮን ስታደርግ በውድድሩ የአውሮፓ ቡድኖችን ለአራት ተከታታይ ጊዜ ሻምፒዮን የሆኑበትን ጉዞ ያስቆመችም ሆናለች።

በዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከ40,000 በላይ ተመልካቾች የታደሙ ሲሆን የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖም ተገኝተዋል።

ኡራጓይ በ1997 እና 2013 በዉድድሩ ለፍፃሜ ደርሳ ዋንጫዉን ማጣቷ የሚታወስ ነዉ።

ብራዚል በ2011 ከደቡብ አሜሪካ የመጨረሻው የዉድድሩ አሸናፊ የነበረች ሀገር ናት።

ከዚህ ጨዋታ ቀደም ብሎ በዉድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችዉ እስራኤል ደቡብ ኮሪያን 3ለ1 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ማግኘት ችላለች።

Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...