Get Mystery Box with random crypto!

#ታህሳስ_19_ኃያሉ_መልአክ_ቅዱስ_ገብርኤል_ሠለስቱ_ደቂቅን_ከእቶን_እሳት_ያዳነበት_ዕለት_ነው። | ዝክረ ብሒለ አበው

#ታህሳስ_19_ኃያሉ_መልአክ_ቅዱስ_ገብርኤል_ሠለስቱ_ደቂቅን_ከእቶን_እሳት_ያዳነበት_ዕለት_ነው።

አይሁድ እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ለተግሳጽ ከፍሎ ለምርኮ ሰጣቸው፡፡ የሚወዷቸውና የሚባረኩባቸው ዕቃዎች (ንዋያተ ቅዱሳትም) ተወሰዱባቸው፡፡ ይህ ለአይሁድ ከባድ ቅጣት ነበር፡፡ በዚህ ደንግጠው ንስሐ እንዲገቡ እግዚአብሔር  ይህን ከደረገ፡፡ እኛም ስናጠፋ እግዚአብሔር በቤተሰብ በኩል፣ ወይም በካህናት አልፎም በሌሎች ሰዎች ይመክረናል፤ ይገስጸናልም፡፡ እኛም ስንቀጣና ስንገሰጽ ልንታረም ይገባል፡፡

ከለዳውያን በዛሬዋ ኢራቅ እና አከባቢዋ የነበሩ ሕዝቦች ናቸው፡፡ በጥንት ዘመን ኃያል መንግሥት አቋቋሙው የሒሳብ፣ የከዋክብት ጥናት፣... ከአስማትና ጥንቆላ ጋር እንደ ትምህርት ይሰጡ ነበር፡፡

ናቡከደነፆር ከ፮፻፭ - ፭፮፪ ዓ.ዓ የነበረ የባቢሎን ንጉሥ ነው፡፡ ይህ ንጉሥ ሁለት ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቷል፡፡ የመጀመሪያው በይሁዳው ንጉሥ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት ሲሆን ፤ ሁለተኛውም በልጁ በሴዴቅያስ ዘመን ነው፡፡(፪ኛ ዜና. ፴፮፥፭-፯፣ ፲፩-፳) በመጀመሪያው ወረራ የግብጽን ንጉሥ ኒካዑን አሸነፈ፡፡ ኢየሩሳሌምንም ያዘ፡፡ እርሱ የበላይ ሆኖ ከአይሁድ ልጆች ነገሥታት ይሾም ነበር፡፡ አይሁድ ሲያምጹ ከተማይቱን አፈራረሳት፤ ቤተ መቅደሱንም አቃጠለ፡፡ ሕዝቡንም ማርኮ ወሰደ፡፡ ኤር. ፵፮፥፪፣ ፪ኛ ነገ. ፳፬፥፩-፯፣ ፪ኛ.ዜና ፴፮፥፲፯-፳፩ ከተማረኩት ወጣቶች ዳንኤልና ሦስቱ ጎደኞቹ አናንያ አዛርያና ሚሳኤል ይገኙበታል፡፡ (ዳን. ፩፥ ፩ - ፯ )

የስማቸውም ትርጓሜ:-
#ዳንኤል_እግዚአብሔር_ዳኛ_ነው
#አናንያ_እግዚአብሔር_ቸር_ነው 
#አዛርያ_እግዚአብሔር_ይረዳዋል
#ሚሳኤል_እግዚአብሔርን_ማን_ይመስለዋል ማለት ነው።

ባቢሎናዊ መጠሪያ ስማቸውና ትርጓሜያቸው:-
#ዳንኤልን_ብልጣሶር_የበኣል_ልጅ (መስፍን) ማለት ነው። #በአል  የባቢሎናውያን ዋና ጣዖት መጠሪያ ነው።

#አናንያን_ሲድራቅ_ሲሉት_የአኩ_አምሳል ማለት ነው #አኩ ባቢሎናውያን የጨረቃ ምላክ የሚሉት ጣዖት ነው

#አዛርያን_አብደናጎ_ይሉታል_የነጎ አገልጋይ ማለት ነው። #ነጎ ወይም ሄቦ የፀሐይ አምላክ የተባለ ጣዖት ነበር፡፡

#ሚሳኤልን_ደግሞ_ሚሳቅ ትርጓሜውም እንደ ሻቅ ማነው ማለት ሲሆን #ሻቅ የመሬትና የውበት አምላክ የሚልዋት ጣዖት ነበረች፡፡
እነዚህም ብላቴኖች ከኢየሩሳሌም ተማርከው በባዕድ ሃገር ሆነው እግዚአብሔር ያመልኩ ትዕዛዙንም ያከብሩ ነበር።

ከዕለታትም በአንደኛው ዕለት ንጉሡ ናቡከደነፆር የእርሱን ትዕዛዝና ሕግ የሚያከብረውን ከማያከብረውን ለይቶ ለማወቅ የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው ። ለወርቁ ምስል ሁሉም እንዲሰግድ እንዲንበረከክ አዘዘ ከእነዚህ ሦስት ሲድራቅ ሚሳቅና አብደናጎም ብለው የሚጠሯቸው የልዑል እግዚአብሔር ብላቴናዎች  በቀር ሁሉም ሰገደ ተንበረከከ።

ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሦስቱን ብላቴናዎች ያመጧቸው ዘንድ አዘዘ ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው። አምላኬን አለማምለካችሁ፥ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? እንግዲውስ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው? ብሎ ተናገራቸው።

ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም እንዲህ ሲሉ መለሱለት ንጉስ ሆይ፥ በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ደግሞም ያድነናል! ነገር ግን፥ ንጉሥ ሆይ፥ እርሱ ባያድነን እንኳን አማልክትህን እንደናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንደማንሰግድ እወቅ አሉት።

የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፥ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፤ እርሱም ተናገረ፥ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት እና እሳቱ ይጥሉአቸው ዘንድ አዘዘ፤ የዚያን ጊዜም እነዚህ ብላቴናዎች ከነልብሳቸው ከነመጐናጸፊያቸው ታስረው እሳት ውስጥ ተጣሉ። ናቡከደነፆር አሟሟታቸውን ሊመለከት ቆመ ወደ እሳቱም ተመለከተ።

አራት ሰዎችም በእሳት ውስጥ ሲመላለሱ አየ ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም። ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን? ብሎ ተናገራቸው። እነርሱም ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው መለሱለት።እርሱም እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ። ይህም ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡
ናቡከደነፆር ድምጹን ከፍ አድርጎ ከእሳቱ እንዲወጡ ተጣራ የራሳቸው ጸጉር አልተቃጠለም ልብሳቸውም እንዲሁ ናቡከደነፆር ከዚህ በኃላ እንዲህ ሲል እግዚአብሔርን አመሰገነ “በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፥ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ” ትንቢተ ዳንኤል ፫፡ ፩- ፴
 
ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፡፡ አሜን!!!