Get Mystery Box with random crypto!

ነፃ የትምህርት ዕድል ! የሳንድፎርድ ኢንተርናሽናል ት/ቤት በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአ | B B C አማርኛ ዜናዎች®

ነፃ የትምህርት ዕድል !

የሳንድፎርድ ኢንተርናሽናል ት/ቤት በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር በሚገኙ የመንግሥት ት/ቤቶች በመማር ላይ ከሚገኙ #በትምህርታቸውና #በፀባያቸው የተመሰከረላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ የነፃ ትምህርት ዕድል ለመሥጠት ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ አሳውቆናል።

ተወዳዳሪ ተማሪዎች ለነፃ ትምህርቱ ውድድር ለመመዝገብ ሲመጡ የሚከተሉትን መስፈርቶች አሟልተው የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት መግለጫ ኮፒ ይዘው መምጣት ይጠበቅባቸዋል።

1. በአ/አ ከሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪ መሆን

2. ተማሪው የተወለደው እ.ኤ.አ ነሐሴ 31/2008 ድረስ 14 ዓመት የሚሞላዉ ነገር ግን 15 ዓመት በታች የሆነ ይህንንም የሚያረጋግጥ የልደት የምሥክር ወረቀት ይዘው መቅረብ የሚችሉ

3. በ2014 የትምህርት ዘመን መጨረሻ የ8 ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አማካይ ወጤት ከ95% በላይ የሆነ

4. የ7ና 8 የክፍል ትምህት ለየብቻው አማካይ ውጤቱ ከ90% በላይ የሆነ

5. ስለመልካም ሥነምግባሩ ወይም ፀባዩ ከሚማርበት ት/ቤት የጽሁፍ ማስረጃ በሳንድፎርድ ተቀባይነት ሲያገኝ ማምጣት የሚችል

6. ት/ቤቱ የሚሰጠውን የመግቢያና ቃለመጠይቅ ፈተናዎችን የተሻለ ዉጤት ማስመዝገብ

7. የወላጅ/የአሳዳጊ ሙሉ ፈቃድ ያገኘ

8. አሸናፊ የሚሆነው ተማሪ በአሥረኛ (10) ክፍል በት/ቤቱ ተመዝግቦ ለመማር ፈቃደኛ የሆነ ናቸዉ።

9. የምዝገባ ሰዓት ጠዋት 2፡30 - 6:00 ከሰዓት ከ7:30 - 9:30

መስፈርቱን ያሟሉ ተማሪዎች ነሐሴ 19/2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ለፅሁፍ ፈተና ይቀርባሉ።

ቦታ፦ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል አካባቢ በሳንድፎርድ ት/ቤት እስከ ነሐሴ 18 ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል።