በመቀለ ከተማ ላይ ተፈፀመ በተባለ የአውሮፕላን ጥቃት 4 ሰዎች መገደላቸውን እና በጥቃቱ ሌሎች 9 ሰዎች መጎዳታቸውን የዓይን እማኞች እና የሆስፒታል ምንጮች መናገራቸውን የጀርመን ድምፅ ዘግቧል። የኢትዮጵያ መንግሥት አየር ኃይል በትግራይ «ወታደራዊ ስፍራዎች ላይ ብቻ ያነጣጠረ» ጥቃት መፈፀሙን አስታወቋል። በሰላማዊ ሰዎች መኖርያ አካባቢ ተፈፅሟል ተብሎ በትግራይ አማፅያን የቀረበበትን ክስም ዉድቅ አድርጓል። @bbc_amharic1 410 views , 11:37