አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ተይዘው ተወሰዱ። የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዘዳንቱን አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ አባላት እና ደጋፊዎቹን፤ ፓሊስ በ3 መኪና ጭኖ እንደወሰዳቸው ገለፀ። ፓርቲው " ክስተቱ የተፈጠረው በሰላማዊ መንገድ የካራማራን የድል በአል ለማክበር በሄዱ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ነው " ብሏል። ከዚህ ክስተት ቀደም ብሎ ፕሬዚደንቱ አቶ እስክንድርን ጨምሮ የባልደራስ አመራሮች የካራማራ የድል በዓልን እንዳያከብሩ ተከልክለው እንደነበረ ፓርቲው ገልጿል። አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ አባላትና ደጋፊዎቹ በአሁን ሰአት በልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንደሚገኙም ፓርቲው አሳውቋል። ክስተቱን በተመለከተ በፖሊስ የሚሰጥ ማብራሪያ ካለ ተከታትለን የምናሳውቅ ይሆናል። @asosaonline 404 views09:11