Get Mystery Box with random crypto!

Arqem[አርቀም]

የቴሌግራም ቻናል አርማ arkemmy — Arqem[አርቀም] A
የቴሌግራም ቻናል አርማ arkemmy — Arqem[አርቀም]
የሰርጥ አድራሻ: @arkemmy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 405
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ በዚያች ይበልጥ መልካም በሆነችውም (መንገድ እና ስልት) ተወያያቸው። (አል ነህል 125)
ለአስተያየቶ @MezidaTemam

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-19 07:35:42 ሙታኗ ላይ ዝሙት ፈፀምኩ
"""""""""""""""""""""""""""""""""
ማንኛውም ሙስሊም ታሪኩን ያንብበው አስገራሚና አስደናቂ እንዲሁም አስተማሪ ታሪክ ነው

ዑመር (ረ.ዐ) ወደ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እያለቀስ ገባ፤ ይህን የተመለከቱት መልዕክተኛውም፦ ምን ያስለቀስሀል ኡመር" አሉት።
አንቱ የአላህ መልዕክተኛ…! በር ላይ አንድ ወጣት ሲያለቅስ ተመልክቼ አንጀቴን አላወስው" አላቸው።

"አንተ ልጅ ሆይ… ለምን ታለቅሳለህ ?" በማለት መልዕክተኛው ወጣቱን ጠየቁት።
የሀፍረት ስሜት እየተስማው፦"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ…ብዙ ወንጀሎች ያስለቅሱኛል የተቆጣብኝ ጌታዬንም ፈርቻለሁ አላቸው ።
ነቢዩ (ሰ.ዓ.ወ) "በአላህ ላይ ሌላን አካል አጋርተህ አምልከሀልን?" አሉት።
አይ…አላቸው።
"ነፍስን ያለ አግባብ ገለሀልን?" አሉት።
"አይ…" አላቸው።
እንግዲያውስ ወንጀልህ የሰባት ስማያት፣ የሰባት ምድርን፣ የተራራዎችን እና የኮረብታዎችን ያህል እንኳ ቢሆን አላህ ይቅር ይልሀል" አሉት።

"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ… ወንጀሌ ከስባት ስማያት፣ ከስባት ምድር፣ ከተራራዎች እና ከኮረብታዎች ይበልጣል እኮ" አላቸው።
"ወንጀልህ ይበልጣል ወይስ ኩርሲይ?" ብለው ጠየቁት።
"ወንጀሌ ይበልጣል" አላቸው።
"ወንጀልህ ይበልጣል ወይስ አርሽ?" ደግመው ጠየቁት።
"ወንጀሌ ይበልጣል" በማለት ደግሞ መለስላቸው።

"ጌታህ መሀርታው ይበልጣል ወይስ ወንጀልህ?" ብለው ጠየቁት።
"አላህ ይበልጣል፣ ይልቃልም" ብሎ መለስላቸው።
"ታዲያ ትልቁንም ወንጀል እኮ ትልቁ አላህ እንጂ ማንም አይምርህም" አሉት

መልዕክተኛው።
"አንተ ልጅ እስቲ ወንጀልህን ንገረኝማ…አሉት
እሱም፦"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ…!ወንጀሌም በእርሶ ፊት መናገር ያሳፍረኛል" ብሎ መለስላቸው።
"እስቲ ወንጀልህን ንገረኝ" ጥያቄውን ደገሙለት።
"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ…! እኔ ቀብር ዘራፊ ነበርኩ
ላለፉት ሰባት አመታት መቃብሮችን ስዘርፍ አሳልፊያለሁ።
ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት የመዲና እንስት ሞታ ቀብሯን በቀን ልዘርፍ ቆፍሬ ከፈኑን ከላይዋለይ ገለብኩት፤ ከፈኗን ይዤ ትቻት መሄድ ጀመርኩ ነገር ግን ብዙም ሳልርቅ ሽይጧን ወደ ቀብሩ እንድመለስ ጎተጎተኝ…! ተመለስኩኝ እና ዘሞትኳት

ከዚያም ተነስቼ መሄድ ጀመርኩ፤ ብዙም ሳርቅ ሙታኗ ብድግ ብላ፦"ዋ ጥፋትህ… አንተ ወጣት…!! ያ ዙፋኑን ለፍርድ አስቀምጦ ከበደለኞች ሀቃቸውን ይዞ ለተበዳዮች የሚያደርስውን ጌታ አታፍርምን
በሙታን አውድማ ብቻዬን ትተህኝ ትሄዳለህን…?
አላህ ፊትም ለሂሳብ ስቆም ከነጀናባዬ አቆምከኝ…! ትርክቱን ሳይጨርስ……

መልዕክተኛው አፋቸውን ይዘው፦"አንተ ፋሲቅ ዞር በልልኝ፤ አንተ ለእሳትም ምንኛ ተገቢ ነህ…!
ወጣቱ ተስፋ ቆርጦ ከመልዕክተኛው ዘንድ ወጣ። ለአርባ ቀናት ያህልም አላህን ሲማፀን ከረመ።
አርባኛ ቀኑ ሲሞላ እጁን ወደ ላይ አንስቶ፦"አንተ የሙሀመድ፣ አንተ የአደም፣ እና፣ የሀዋ ጌታ ሆይ… ፀፀቴን ተቀብለህ ምረህኝ እንደሆን ለሙሀመድና ለባልደረቦቹ አሳውቅልኝ።

ያ-ሳይሆን ቀርቶ ፀፀቴን ያልተቀበልከኝም እንደሆነ፤ ከስማይ እሳት አውርደህ አሁኑ አቃጥለኝ'ና ከጀሀነሚቱ እሳት ገላግለኝ" በማለት አላህን ተማፀነ።
ፈጣኑ መልዕክተኛ , የረሱል (ሰ.ዓ.ወ) ባልደረባ ጅብሪል (ዐ.ስ) ሰማያትን አቋርጦ ወደ ነብዩ ( ሰ.ዓ.ወ) ዘንድ የጌታውን ትዕዛዝ ይዞ ብቅ
አለና፦

ሙሀመድ ሆይ…! ጌታህ ስላም ይልሀል" አላቸው።
ነቢዩም (ሰ.ዓ.ወ ) ፦"እሱ ስላም ነው፤ ስላምም ከሱ ነው፤ ወደሱም ተመላሽ ነው" ብለው በንግግር ተጠበቡ።

"አላህም ብሎሀል (ፍጥረትን አንተ ነህ እንዴ የፈጠርከው)" አላቸው ጅብሪል።
"እንዴታ…! እኔን እና ፍጥረታትን በሙሉ የፈጠረው ጌታ ነው የፈጠራቸው)" በማለት መለሱ።
"ጌታህም ይልሀል (አንተ ነህ እንዴ መሀርታን የምትለግስው)" ዳግም ጅብሪል ጥያቄያዊ መልዕክቱን አስተላለፈላቸው።
"እንዴታ…! አላህ እኮ ነው እኔንም ፍጥረታትንም ይቅር የሚለው መሀርታ የሚለግስው" በማለት መለሱ።
አላህም ይልሀል (ባርያዬን ይቅር በለው፤ እኔም ይቅር ብየዋለሁ)" በማለት ጅብሪል የጌታውን መልዕክት አስተላለፈ።

ይሄን ጊዜ መልዕክተኛው ያን ወጣት በማስጠራት አላህ ይቅር እንዳለው አበስሩት።

በማያልቀው የአላህ አጅር ተጠቃሚ ትሆኑ ዘንድ ላይክ ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመዶ ያካፍሉ

♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ

@ArkemMy

@ArkemMy
@ArkemMy

@ArkemMy
98 viewsHope ➊ ye aryifochu , 04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 10:37:36 ሴት ልጅ ከቤቷ ውጭ ለበእድ ወንዶች
ተኳኩላና ተበጃጅታ ከወጣች ከእሷ ዘንድ መልካም ነገር የለም
እንዲሁም ተኳኩላ ስትወጣ እያዩ ዝም የሚሉ ወንዶች እነሱ ዘንድ መልካም ነገር የለም ምክንያቱም እነሱ ደዩስ (ቅናት አልባ) ወንዶች ናቸውና ቅናት አልባ ወንድ ደግሞ ጀነትን አይገባም

♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ

@ArkemMy

@ArkemMy
@ArkemMy

@ArkemMy
220 viewsHope ➊ ye aryifochu , 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 13:24:13
ነጭ ጀለቢያ የለበሱት ማን እንደሆኑ ታውቃለህ
ሲታዩ ተራ ሰው ይመስላሉ ኣ ግን አይደሉም ቢፈልጉ ንጉስ መሆን የሚችሉ ነበሩ
ግን ......
እኚህን አዛውንት የሳውዲ አረቢያ የመጀመሪያው ንጉስ ልጅ የንጉስ ሳልማን
ወንድም ልዑል ማምዱህ ቢን አብዱል አዚዝ አል ስዑድ ናቸው።
ህይወታቸውን በሙሉ ለቅዱስ ቁርኣን አገልግሎት የሰጡ በህይወት ዘመናቸው
ወደ 70,000 ለሚጠጉ ተማሪዎች ቅዱስ ቁርኣንን ያስተማሩ።
የታቡክ ግዛት ገዥ ሆነው ተሹመው ግን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ስልጣን
አልፈልግም በማለት ስልጣናቸውን የለቀቁ።
# አጂብ የዱንያን ንግስና ያልፈለጉ ለአኼራ የሰነቁ # ድንቅ ሰው ረጅም እድሜ
ከአፊያ ጋ ይስጥዎ
@ArkemMy
@ArkemMy
@ArkemMy
427 viewsHope ➊ ye aryifochu , 10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 22:47:47 #እባክሽ
:
:
ትናንት ባማን ደና በሚያስቀና ለዛ፣
ሆነን አቻ ላቻ ያበጀነው ታዛ፣
ቀን በገፋ ቁጥር የኋላ የኋላ፣
ዘመም እዳይልብን በዳዋ እንዳይበላ፣
ዘላለም እንዲከርም የልባችን ምግብ ሆኖ በአንድ ትሪ፣
ባክሽ የኔ ፍቅር ሰው መምሰሉን ትተሽ ሰው መሆን ጀምሪ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@ArkemMy
@ArkemMy
@ArkemMy
@ArkemMy
201 viewsHope ➊ ye aryifochu , 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 15:12:44 እንደዚህ ተፈላስፌ Join አስብያቹ ተመልሳቹ ትወጣላቹ ኧረ አስብልኝ በልመና ሳይሆን በፍቅር አብራቹን ቆዩ
193 viewsHope ➊ ye aryifochu , 12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 13:13:39 ከትውስታ
እንዲህ ነበርን

ሰው ሰው እሚመስለው፣ በስብእናው ቢሆን፡፡


ውስጡ በታጨቀው፣ ለብሶ ሰውነቱን
ቀንድ፣ ጭራ ኑሮት ፣ ግማሹ ያዳም ዘር
ሰው መሆኑ ቀርቶ፣ አውሬ ይሆን ነበር
(መዚዳ ተማም)

ሌሎች ግጥሞች እንዲደርሶ
@ArkemMy
177 viewsHope ➊ ye aryifochu , 10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:43:34 ትልቁን ምክንያትክን አዘጋጅ

ገና በጠዋት ከእንቅልፍክ ከመነሳትክ ድክም ብሎክ ተኝቼ አይደለም እንዴ ያደርኩት የሚያስብል አጋጣሚ ኖሮክ ያውቃል? እናቶቻችን አባቶቻችንና አያቶቻችን ከኛ ምንም ያክል በእድሜ ከፍ ቢሉም ግን ባላቸው ጉልበትና ብርታት ሁላችንም በጣም እንገረማለን ከየት አመጡት? ሁሉም ቢጠየቁ የሚሰጡት ምላሽ የሚሆነው ትልቅ ምክንያት ስላለኝ ነው የሚል ነው!

አንተ አዎ አንተ ልጃቸው ነህ ትልቁ ምክንያታቸው ላንተ ሲሉ ግዴታ መበርታት አለባቸው ስለዚህ አንተም ምክንያት ይኑርክ ትልቅ ምክንያት አዘጋጅ ያኔ በፍፁም መድከም አይፈቀድልክም

መልካም ዕለተ ሰንበት ተመኘን
የእናንተው ምርጥ ጓደኛ

https://t.me/ArkemMy
320 viewsHope ➊ ye aryifochu , 09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:14:45 ማመስገን አታቁም!

የጎደለህን አትቁጠር የተሰጠህን አስብ፤ ብዙ ያልጠበካቸው መልካም ነገሮች በህይወትህ ብዙ ጊዜ ደጋግመው ተከስተዋል፤ የዛሬው ቀን አንዱ ስጦታ ነው።

ትናንት ሲስቁ ውለው ዛሬ ጠዋት ግን ከእንቅልፋቸው ያልነቁ ብዙ ሰዎች አሉ፤ ይሄንን ፅሁፍ ለማንበብ ቢያንስ መተንፈስ አለብህ፤ በህይወት እስካለህ ደግሞ የማይስተካከል ነገር የለም። ወዳጄ መስጠት ለማይሰለቸው ፈጣሪህ ማመስገን አትሰልች!

https://t.me/ArkemMy
132 viewsHope ➊ ye aryifochu , 09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 09:08:21 #ረሱል ﷺ መንገድ ዳር አፈር እየጫሩ ቁጭ ብለው አሸዋ ጫር ጫር እያደረጉ በሀሳብ ተጉዘው ተከዙ ምነው ያረሱለላህ ﷺ ሲሏቸው?
በጣፋጭ አንደበት እንዲህ ሲሉ መለሱ
"ኢሽተቅቱ ኢላ ኢኽዋኒ"
እኔ ወንድሞቼ ናፈቁኝ ከኔ ቡሃላ የሚመጡ አማኞች ናቸው እኔን ሳያዩ ያመኑብኝ .. ወንድሞቼ ናፈቁኝ

ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያረሱላለህﷺ
ፊዳከ ሩሂ ወደሚ ያሀቢበላህﷺ
132 viewsHope ➊ ye aryifochu , 06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-10 00:07:50 የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል

''ከእናንተ መካከል አንዳቹ ሰላት የሰገደበት መስገጃዉ ላይ እስካለ እና ዉዱእ እስካላጠፋ ድረስ መላኢኮች በርሱ ለይ ሰለዋት ያወርዱለታል። ''አሏህ ሆይ ወንጀሉን ማረዉ: አሏሀሰ ሆይ እዘንለት።'' ይላሉ።''

@ArkemMy
165 viewsHope ➊ ye aryifochu , 21:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ