2022-06-13 20:57:56
ተስፋ_ያጣች_ሴት
እውነተኛ እና አስተማሪ ታሪክ
#ክፍል_12
መመረቅ አንዴ ነው እንዲሉ የሀና እድል ስትወለድ ጀምሮ
መከራና ስቃይ አቅምና ሁኔታውን እየቀያየረ ያሰቃያታል፤
ያለፈው ፈተናዋን ስታልፍ ሌላ ፈተና ይገጥማታል፤ አሁን
ደግሞ ይባስ ብሎ ዘመድ በሌለበትና አንድም ሰው
በማታውቅበት ቦታ አበደች በርግጥ ሀናን በረንዳ
ማደሯንና ብቻዋን መለፍለፏን ላላየ ጤነኛ ትመስላለች
ምክንያቱም ጨርቋን አልጣለችም ...ይህ በእንዲህ
እንዳለ ከሀና ፍቅር ይዞት የነበረ እሷ ሴተኛ አዳሪ
የነበረችበት ሆቴል በሼፍነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት
ፀበል ወሰዳት... ይሄኔ ነበር በቅናት መንፈስ ተነሳስተው
ሀናን ለእብደት የዳረጓት አብረዋት ይሰሩ የነበሩት ሴቶች
እንደሆኑ የታወቀው ...
ከ3 ወር ቡሃላ ሀና ትሽሏት ሀዋሳን ለቃ በድጋሚ አዲስ
አበባ ተመለሰች ይሄኔ ፀበል ወስዶ እንድትድን የረዳት
ቅዱስ አብሯት ነበር ሀና ቅዱስን እንደወንድም ወደደችው
እሱ ግን ያፈቅራታል ነገር ግን ፍቅሩን አልገለፀላትም
ነበር እሷም ከዛ ቀን ቡሃላ ገላዋን ሽጣ መኖር
አልፈለገችም ነበርና በቅዱስ እርዳታ ቤት ተከራይታ
መኖር ጀመረች ግን ሁሌ የሱን እጅ ማየት ስላሳፈራት
ከእናቷ ቤት አካባቢ የሚገኝ የቡና መልቀምያ ድርጅት
ውስጥ ተቀጠረች በዚ ግዜ ስለእናቷም ወሬ ታጠያይቅ
ነበር የሰማችው ዜና ግን ሀናን በሰአቱ በጣም ረብሿት
ነበር ... እናቷ አፀደ የምታውቀው ልጇ ውጪ ሀገር
ማለትም አረብ ሀገር እንደሄደች ነው ይህን እንድታስብ
ያሳመናት ደግሞ የሀና እንጀራ አባት መሆኑንም
ሰምታለች ...
ታድያ አንድ የተባረከ ቀን የሀና ስልክ ጠራ የውጭ ስልክ
ነበር አንስታም "ሀሎ" ስትል ይደውላል ብላ
ያልጠበቀችው ሰው ነበር ሀና ልቧ ስንጥቅ አለ ይሄ
ድምፅ ከረጅም ግዜ በፊት ልክ እንዳሁኑ ስትሰማው ሌላ
ስሜት ይሰማት ነበር ኪሩቤል ነው ማመን ተሳናት
ኪሩቤልን ባሳለፈቻቸው ግዜያቶች ሁሉ ከ100 ቢያንስ
95ቱን ቀናት ታስበው ነበር ሳታስበው እምባ ተናነቃት
ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላም "ሀኒ አፈቅርሻለሁ!! ብዙ
ጠብቄሽም ነበር በኔ ምክንያት ፀንሰሽ ... ህይወትሽ
እንደተበላሸና ከቤት እንደጠፋሽ ሰምቻለው ግን ፈልጌ
አጣሁሽ ይቅር በይኝ እባክሽ..." አለ እንባ እየተናነቀው
እንዳወራ ድምፁ ያሳብቅ ነበር ሀናም መናገር አቃታት
እንባዋ ያለገደብ ፈሰሰ ምንም መልስ ሳትሰጠውም
ዘጋችበት... ቅዱስ ተቀምጦ ያያት ስለነበር ልክ ስልኩ
ሲቋረጥ ነገሩን ለማወቅ እንደጓጓ ሁሉ የሀናን አይኖች
እየጠራረገ ጠየቃት... ሀናም እንደምንም እራሷን
አረጋግታ ስለኪሩቤል ነገረችው ቅዱስም ያፈቅራት
ስለነበር በኪሩቤል ቀና ግራ በሚያጋባ አኳኋንም
"...ታፈቅሪዋለሽ ማለት ነው?" ሲል ጠየቀ ሃናም የረጠቡ
አይኖቿን እያደራረቀች "አላውቅም እኔ የማውቀው አሁን
ከጎኔ ቢሆን ደስተኛ እንደምሆን ብቻ ነው" አለች።
ኪሩቤል ከሰአታት ቡሃላ ደግሞ ሲደውል ሀናም ተረጋግታ
ስለነበር በደምብ አወሩ እሱም ጀርመን እንደሄደ ነገራት
... ከዛ ቡሃላ ሁሌም ይደውላል ልጁን በማስወረዷ
እንደተናደደባት ደጋግሞ ይነግራታል ሀና ግን ከሱ ቡሃላ
በጌታቸው ስለመደፈሯም ሆነ ስለ ሴተኛ አዳሪነት
ህይወቷ ፈፅሞ አልነገረችውም ታማ ፀበል እንዳሻላት
ብቻ ነግራው አዝኖ ነበር ... ከዛም ሀናን ፓስፖርት
እንድታወጣ ነገራት ሀናም ፓስፖርት አውጥታ ወደ
ኪሩቤል ጀርመን ለመሄድ ፕሮሰስ ጀመረች ቅዱስንም
የግሉ ቤት እንዲፈልግ ነገረችው ቅዱስ ግን "እስካለሽ
አብሬሽ እሆናለው" አላት ሀናም ቅዱስ ውለታ ስለዋለላት
እንደወንድሟ ትወደዋለች እንደሚያፈቅራት ግን እስካሁን
አልገለፀላትም ይሁንና ቅዱስ የሀናን መሄድ
አልወደደውምና እንድትቀር ለማድረግ እንቅፋት ያዘጋጅ
ጀመር...
ኪሩቤል ስለቅዱስ ምንም አያውቅም ቅዱስ ግን
ስለኪሩቤል ሁሌም ይሰማ ነበር ሀናም ይህችን ሀገር
ተሰናብታ የምትሄድበትን ግዜ በጉጉት ትጠባበቅ ነበር
ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድ ቀን ምሽት ቅዱስ ሀና
ኢንባሲ ሄዳ እስክትመጣ ቤቱን አሰማምሮ እራትና የወይን
መጠጥ አዘጋጅቶ ጠበቃት ሀናም ይህን ማሰቡ ደስ
እያላት በሉ ከዛም ወይን ቀድቶ ሰጣት... ሀና የመጠጣት
ልምድ ነበራት ማለትም ቶሎ አሰክርም ነበር ያን ቀን ግን
አንድ ብርጭቆ ሳትጨርስ ሰከረች ይህንም አጋጣሚ
ቅዱስ ተጠቀመበት... ሲነጋ ሀና እራሷን አሟት ነበር
ኪሩቤል ይደውላል ብላ ቅትጠብቀው ሳይደውል ቀረ ያ
ቀን እንደምንም ነጋ... ግን ኪሩቤል አልደወለም
በሳምንቷ እራሷ ካርድ ሞልታ ደወለች ኪሩቤል ግን
"ሁለተኛ እንዳትደውይ" ብቻ ብሎ ዘጋባት... ሀና ይህን
ማመን ተሳናት ኪሩ ይህን ለምን አረገ ብላ እራሷን
ጠየቀች ግን ምንም መልስ አጣች ሀና ተስፋዋ ባንዴ
ድራሹ ጠፋ...
ክፍል #13 ይቀጥላል.....
https://t.me/Arif_leboled
1.1K views17:57