Get Mystery Box with random crypto!

አሁናዊ መረጃ! የትግራይ ወራሪ ሀይል በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ወረዳ በር ማሪያም በሚባለው | Abissiniya Empire #አማራ

አሁናዊ መረጃ!

የትግራይ ወራሪ ሀይል በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ወረዳ በር ማሪያም በሚባለው አቅጣጫ በዚህ ቅፅበት ተኩስ የከፈተ ሲሆን የወገን ጦርም ወረራውን ለመመከት ውጊያ ጀምሯል። የዛሬውን ጨምሮ አሸባሪው ቡድን  አማራ ክልልን ለመቆጣጠር በአራት ዞኖች ማለትም ሰሜን ወሎ ዞ፤ዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን፤ሰቲት ሁመራ ዞን እና በሰሜን ጎንደር የዞን አሰተዳደር ሰር በሚገኙ ወረዳዎች ውሰጥ ግንባር ፈጥሮ እየተዋጋ ይገኛል።

አሸባሪው ቡድን የአማራ ክልልን አስተዳደራዊ ወሰን በሀይል ጥሶ ለመግባት ጦርነት ከመክፈቱ በተጨማሪ እድል ቀንቶት በተቆጣጠረው አካባቢ የሚገኙ ህዝቦችን እየገደለ፤ንብረት እየዘረፈ፤ሀብት እያወደመ ነው። ይሁን እንጅ አቅሙ በፈቀደው መጠን የአማራን ህዝብ ለማጥፋት እየጣረ መሆኑ ግልፅ ሆኖ ሳለ ከህዝቡ ከባድ አፀፋ ሲገጥመው ፀባችን ከብልፅግና መንግስት ጋር እንጅ ከአማራ ጋር አይደለም የሚል የተለመደ ማደናገሪያ ፕሮፓጋንዳውን መንዛት ጀምሯል።