Get Mystery Box with random crypto!

'ናፊባ' ክፍል ~ ሠማንያ አምስት በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888 'ሙሉ አዳር አልወጣም። ሲመስ | የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

"ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ አምስት
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"ሙሉ አዳር አልወጣም። ሲመስለኝ መርዶው አልተነገረውም። የዋና ሳጅኑን መሞት ቢሰማ ኖሮ አስችሎት አይቆይም!" አለ የራሱን ፀጉር በጣቶቹ እየመነሸረ። ከእንቅልፍ መባነኑ እንዳይታወቅበት በተቻለው መጠን ሳይተኛ እንዳደረ ለማሳወቅ እየጣረ።" ተኝተህ በነበረበት ስአት ሄዶ ከሆነ ግን እኔ የለሁበትም!!" ንዴት የተቀላቀለበት ዱብዳ አነጋገር "ኧረ በጭራሽ ለሰከንድ ያህል እንኳን ልተኛ አላንቀላፋሁም።አይኔንም ከበራቸው አልነቀልኩም"አለ "እሺ ብቻ ለቅሶው ጋር ቀድሞህ ከተገኘ የሚያሳውቀኝ ሌላ አባል አለ" ብላ አስፈራራችውና ስልኩን ዘግታ አዲስ ነገር እንዳለ ለማወቅ ስልኳን ወደሌላኛው አሻንጉሊቷ ደወለች። የስልክ ተቀባይዋም ስልኩን አንስቶ ምንም ነገር እንደሌለና እስካሁን እንዳልመጣ ሲነግራት ከጥርጣሬዋ በመላቀቅ እፎይ አለች። ጥርጥሬ እንደምግብ የምታመሰኳው ነገር ነው። ለእሷ እያንዳንዱ ድርጊት ትልቅ ትርጉምና ዋጋ አለው። ይህን ምስጢራዊ ቡድን በሀላፊነት ስትመራ እያንዳንዱ ሰራተኛዋን በጥርጣሬ ነው የምትመለከተው። አንዳቸውንም የውሸት እንጅ የእውነቷን አታምናቸውም። ሁሉም የግቧ መውጫ መሰላላቸው እንጅ ሌላ አንዳች ጥቅም የላቸውም። ለዚህም በእነሱ ፊት ኮስታራ ፊቷን ነው ሰርክ የምታሳያቸው። አሁን ላይ ግን በርካታ ሰራተኞቿን በሞትና በክህደት ካጣች በኋላ ውስጧን ፍርሃት ቢገባውም ፍርሀቷን ግን በእነሱ ፊት አታሳይም።ቀን በቀን በወንድሟ እየተሳደደችም ፅንፍ ህልሟን ለማሳካት ማንኛውንም ነገር ማድረግ እንዳለባት አውቃለች። በጥንቃቄና በብልሀት የተወጠሩት የሚሽን ክሯቿ ለመበጠስ እየመነመኑ ቢመስሉም ነገር ግን እሷ በፍፁም ተስፋ አልቆረጠችም። ነገር ግን ግማሽ ነፍሷ የተሸነፈች እንደሆነ ይነግራታል። ቢሆንም እስከመጨረሻው ድረስ እታገላለሁ በሚል ፅኑ ፍላጎት መንገዷን ቀጥላለች።
*****
ንጋት ከጨለማ ወስዶ መልዕይተ ቀኑን ለፀሐይ ካስረከበ በኋላ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በማለዳ ቢነቃም ሀዘን እንዳጠላበት ነው። እስካሁን ፊቱ በጭራሽ የነቃ አይመስልም። የክብር ልብሱን አንድ በአንድ ከለበሰ በኋላ "በል ተሕሚድ ውሎዬ ለቅሶ ላይ ነው የሚሆነው።አንተ እንግዲህ የተለዬ ነገር ለማንኘት ሞክር የቻልከውን ያህል ጣር። ይሄ ሊሆን ይችላል ብለህ የጠረጠርከውን በሙሉ በማስታወሻህ ይዘህ ጠብቀኝ።የሕይወቴ ፈታኙና እጅግ ልዩ ትርጉም ያለው ምርመራዬን ነው የተጋራኸኝ። ከአንተ የሚጠበቀው ጥርጣሬዎችህነ ባገኘኽበትና ባሰብክበት ልክ ማስፈር ነው የሚጠበቅብህ ሌላ ከአንተ ምንም አይጠበቅም።ብሎ ትከሻውን መታመታ አድርጎት ትቶት ወጣ ።
ሸዋንግዛው በሀሳብ ውስጥ ትክዝ እንዳለ ነው። በአንዳች ነገር ክንፉ ተሰብሮ ዋጋ ቢስ የማይረባ ንስር ስነልቦናን ሀያ አራት ስአት ባልሞላ ጊዜ ተላብሷል። አቅሙ እስከዬት እንደሆነ የነገሩት መሰለው። የነዚህ ምስጢራዊ ሰዎች ማንነትና ምንነት የውሃ ሽታ ሆነበት። ሁኔታው ከአቅሙ በላይ እንደሆነ እንዲያውቅ አውቆም እንዲያምን ያደረጉት መሠለው።በዚህ ሁሉ የራስ ጥያቄና መልስ ተወጥሮ ባለበት ዝም ብሎ የመሀሉን ስፖኪዮ ሲመለከት ከኋላው ባለ አንድ ቅያስ ላይ መኪና ቆሞ ተመለከተ። ሽጉጡን ከመሳቢው አቀባብሎ በማውጣት ቀስ አድርጎ ማርሹ ጋር ያለበት ክፍት ቦታ ቀስ አድርጎ አስቀመጠው። ሰረቅ አድርጎ ወደ ኋላ እየተመለከተ "እነዚህ ውሾች እኔንም እየተከታተላችሁኝ ነበር? የማትረቡ ብሎ ሊዞር ሲል አይኑ ላይ አንድ ነገር ተመለከተ። የሚከታተለው መኪና ላይ "ዓደይ ሞል" የምትል በራሪ ወረቀት ነገር የመኪናው መስታውት ላይ ተመለከተ። የምፀት ፈገግታ ፈገግ አለና "መች አጣኋችሁ የዚህን ሰው ማንነትና ምንነት ያወኩ ጊዜ ያኔ እኔ ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው አይደለሁም ልጆቼን ይንሳኝ!" አለ ከንፈሩን ንክስ እያደረገ።
********
ሲሐም ኤሌዝንና ብሩክታዊትን ትምህርት ቤት አድርሳ ከመጠች በኋላ ተሕሚድን ትተሻሸዋለች።"ኧረ ተይ የኔ ፍቅር ኢንስፔክተር በጣም ትልቅ ሀላፊነት ነው ሰጥቶኝ የሄደው"አለ የሚሰራውን ስራ አቁሞ አይኖቿን በስስት እየተመለከተ። " ትንሽ ጊዜ ብቻ ነው እኮ።ከዛ ስራዬን ስጨርስ ምንም ችግር የለውም።የፈለግነውን ጊዜ አብረን እናሳልፋለን"ብሎ ወደስራው ሊዞር ሲል ሲሐም መላፋቷን ስትቀጥል ትሕሚድ ቦግ አለበትና "እየነገርኩሽ አይደል ሲሓ! ምንድን ነው እንደ ህፃን ልጅ የምታዳግሚኝ"ብሎ ኮስተር አለባት። "እና ልትቆጣኝ ነው?" አለች እሷም ከመቅፅበት ኩስትር አለች። "የምገላው ባህሪሽ ይሄን ነው።በተደጋጋሚ ነግሬሻለሁ።ከዚህ በኋላ ግን ደግሜ አልነግርሽም እንዳታስቢው እሺ"አለና ዝም ብሎ ወደ ላፕቶፑ አይኖቹን ላከ። ሲሐም ጥፋቷ ታውቋት ይሁን በተሕሚድ ተናዳ በውል ባታስታውቅም እየተመናቀረች ክፍሉን ለቃለት ወጣች። የእሷን መውጣት ተከትሎ ትንሽ ጊዜ ከቆዬ በኋላ በሩን ከውስጥ ቆለፈው። መዘጋቱን የተመለከተችው ሲሐም ይበልጥ በመናደድ "ቆይ አሁን በሩን መዝጋት ምን ይሉታል?" ብላ አጉተመተመች።
********
በርካታ የፖሊስ መኮንኖች፣ የፖሊስ አባላት፣ የፌደራል ፖሊሶች፣የደህንነት ተወካዮች ሰቪሎች እና ሲቪሎች እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት ከሆስፒታል የአስከሬን የማውጣት ስነስርአትና በክብር እየተደረገለት ይገኛል። ሁሉም ፊት ላይ አንዳች ሀዘን ይነበባል። በተለመደው ዝግጅት በስነስርአት አስከሬኑ ወደ መኖሪያ ቤቱ ተሸኝቶ ዘመድ አዝማድ የስራ ባልደረባዎችና ጓደኞች በተገኙበት የማስተላለፍ ስራ ከተሰራ በኋላ የሁሉም የፖሊስ የደህንነትና የወንጀል ምርመራ ክፍል እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ ለስብሰባ እንዲገቡ የፍትሕ ምኒስቴሩና የደሕንነት ኃላፊው ለሁሉም መረጃውን አደረሰ።
ጥሪ የተደረገላቸው የስራ ሀላፊዎች ሁሉም ተገኝተው ስብሰባው መካሄድ ሲጀምር ሁሉም በየተራ ሀሳብና አስተያየት መስጠት ጀመረ። ሰብሳቢዎቹም ፍፁም በሆነ መረጋጋት የተፈጠረው ነገር ምንም ሳይመስላቸው ፊታቸውን አለስልሰው ልባቸውን አደንድነው ስበሳባቸውን ማካሄድ ቀጠሉ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለአንድ ሀያ ደቂቃ ስብሰባው አብ የሚል ነገር ያለው እስኪመስለው ድረስ ቢቆይም ነገር ግን። ዝም ብሎ ሁኔታውንና ድርጊቱን ውሃ ለመቸለስ ለማቀዝቀዝ እንደሆነ ሲረዳ የደህንነት ምኒስቴሩ ለአስተያየት ሰጪዎች እድል በሚሰጥበት ጊዜ እጁን አውጥቶ እድል ከተቀበለ በኋላ የደህንነት ምኒስቴሩን ይሁንታ ሳያገኝ መናገር ጀመረ። ሁሉም በድንጋጤ ዞረው ተመለከቱት "እስካሁኑ ደቂቃ ዴረስ በትዕግሥት ስጠባበቅ ነበር። ምን አልባት ሄደን ከምንሰራው ስራ በላይ የበለጠ ቁምነገር ካለ ብዬ ነበር የተቀመጥኩት። እንጅ የፖለቲካ ሽኩቻውንና አንድ ነገር በተፈጠረ ቁጥር ስብሰባ የምትሉት ነገር በጣም ይሰለቻል። ትላንት ንፁሀኖች ሲሞቱ ነበር።ዛሬ ደግሞ ይሄው ቢሯችን ላይ ገብቷል።ዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስ ከወራት በፊት ልክ እንደኛ የንፁሀን ደም ደመክልብ ሆኖ እንዳይቀር ለዘመዶቻቸው ደግሞ ፍትህን ለማስገኘት ሌት ተቀን ሲሰራ የነበር ጓዳችን ነበር። ነገር ግን በዚህ ስአት እሱም የነዛ ምስኪን ዜጎች እጣ ፈንታ ደርሶት እሱም አርፏል። እኛ ደግሞ አሁንም በቸልተኝነት ስብሰባ ላይ ተቀምጠን የማይሆነውንም የሚሆነውንም እያወራን ነው። ይቅርታ እኔ በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኜ ስብሰቤውን መቀጠል አልችልም!" ብሎ .......

@amba88