Get Mystery Box with random crypto!

አፍሪካ ጊቢ ጉባዔ

የቴሌግራም ቻናል አርማ africagibigubae — አፍሪካ ጊቢ ጉባዔ
የቴሌግራም ቻናል አርማ africagibigubae — አፍሪካ ጊቢ ጉባዔ
የሰርጥ አድራሻ: @africagibigubae
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 176
የሰርጥ መግለጫ

"እረኛ በጎቹን ይሸጣል ክርስቶስ ግን ስለ በጎቹ ተሸጧል ፣ እረኛ የበጎቹን ሥጋ ይበላል የክርስቶስን ሥጋ ግን እኛ በጎቹ እንበላለን ፣ እረኛ የበጎቹን ቆዳ ይለብሳል ክርስቶስ ግን ስለ በጎቹ ዕርቃኑን ተሰቅሏል "

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-08-06 18:34:08 ሰላም ውድ የግቢ ጉባኤያችን አባላት በቅድሚያ እንኳን አደረሳቹ እያልን፥የምንገለገልበት ደብር(ደ/ሰ/ቅ/ እስጢፋኖስ)መጠለያዎቹ ለሱባዔ ስለሚውሉ ከዚህ በኋላ ከነገ ቅዳሜ 1/12/2013 የፍልሰታ ጾም እስከሚያበቃበት እለት ድረስ ሲሰጥ የቆየው ተከታታይ የኮርስ መርሐግብር በምንማርበት ትምህርት ቤት ውስጥ ስለሚሰጥ እየተገኛቹ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ሰናይ ምሽት!
493 views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-18 17:52:07
556 views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-16 21:37:58
468 views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-06-19 11:51:18 ሰላም እንደምን አረፈዳቹ?ዛሬ መንገድ በመዘጋጋቱ እና በአንዳንድ ምክንያት የነበረን የኮርስ መርሐግብር መሰረዙን ከይቅርታ ጋር እንገልጻለን።
658 views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-06-10 12:23:41 "ሰው ጸሎትን በተወ ጊዜ የሞት መሣሪያውን መስራት ይጅምራል።" ቅዱሳን አበው
ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ የእግዚአብሔር ቤተስቦች ነገ የተለመደው የጸሎት መርሐግብር ስለሚኖር 6:30 ላይ ተገኝታቹ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
መልካም ቀን!
703 views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-06-03 19:35:21 "ጸሎት ለሚወዱ ሰዎች እግዚአብሔር ያድርባቸዋል... መከራ ከሚመጣባቸው ከሚያሳዝናቸው ከሰይጣን ያሳርፋቸዋል።" አረጋዊ መንፈሳዊ
ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ የእግዚአብሔር ቤተስቦች ነገ የተለመደው የጸሎት መርሐግብር ስለሚኖር 6:30 ላይ ተገኝታቹ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
ሠናይ ምሽት!
739 views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-21 23:06:08
657 views20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-14 20:54:25 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ።
"ቃለ እግዚአብሔር የገነት ፍሬ ነው።የገነት ፍሬ የእግዚአብሔር ገንዘብ ነው።እግዚአብሔር ደግሞ በከንቱ አልፈጠረውም።" ሊቀ ትጉሃን ኃይለ ጊዮርጊስ ዳኜ

ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ ዉድ የጊቢ ጉባኤያችን አባላት ነገ ቅዳሜ ከ6:30 ጀምሮ የተለመደው የኮርስ መርሐግብር እንዲሁም የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ወርሃዊ በዓል ስለምንዘክር ሌሎች እኅትና ወንድሞቻችንን አስታዉሰን እኛም ተነሳስተን መጥተን የበረከቱ ተካፋይ እንሆን ዘንድ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን ።
-መልካም ምሽት-
581 views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-09 02:19:34 ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#የልደትሽ_ቀን_ልደታችን_ነው

" እንኩዋን ለ2013 ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ "

"ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ::"
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን)"

የብርሃናት ንጉሥ ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመውለድ ዛሬ የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም በእውነት ተወለደች ። ከሊባኖስ ተራሮች ርግብ ጸዐዳ ተወለደች ፤ በሔዋን ምክንያት የተዘጋው የሕይወት መንገድ ይከፈትልን ዘንድ የሕይወት እናት ዛሬ ተወለደች፡፡ የዓለም ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመብርሃን ዛሬ ተወለደች፡፡

የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::

ኢያቄም እና ሐና ዳግሚት ሰማይ ተብላ የተጠራችውን ድንግልን ወለዱ ፤ እውነተኛው ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመ ፀሐይ (የፀሐይ እናት) ቅድስት ድንግል ዛሬ ተወለደች ፤ ብርሃንን ለማስገኘት መወለድ መታደል ነው፤ ከሰው ልጆችም መካከል መመረጥ ዕፁብ ድንቅ ነው፤ የመድኃኔዓለም እናት ለመሆን መወለድ ሰማያዊ ፀጋ ነው።

እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. ፩÷፱)

ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ፪፻፳፮(2,026) ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. ፬÷፰)

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::

ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::

ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::

የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዳያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::

ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ፵ ቀናትም ሲጸልይና ሲማልድ ቆየ:: በ፵ኛው ቀን ፪ቱም ሕልምን ያልማሉ::

እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::

እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ፯ ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::

በ፯ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ ፯) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::

እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)

"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. ፩÷፱)

✞ እመቤታችን ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች::✞

የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:--ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:--ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::

የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::

በእውነት እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር ልዩ ስጦታ ናት። ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመብርሃን ዛሬ ተወልዳልናለችና በእዉነት ደስ ይበለን እልልም እንበል።"

- ወስብሐት ለእግዚአብሔር -

@Africagibigubae
@Africagibigubae
544 views23:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-03 07:00:06 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን
በዐቢይ ሀይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዝኤሰ
ኮነ
ፍሰሃ ወሰላም

#ከትንሣኤ_እሁድ_በኋላ_ያሉ_ዕለታት_ስያሜ፡-

✞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

✞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. ፳ ፥ ፳፯-፳፱

✞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

✞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

✞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

✞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

✞ እሁድ- #ዳግማ_ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

@Africagibigubae
350 views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ