Get Mystery Box with random crypto!

💠 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው።

የቴሌግራም ቻናል አርማ afe_werk — 💠 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው።
የቴሌግራም ቻናል አርማ afe_werk — 💠 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው።
የሰርጥ አድራሻ: @afe_werk
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 568
የሰርጥ መግለጫ

🇬🇳 በዚህ ቻናል ተሰምተው የማይጠገቡትን የአባታችንን
🌈 ተግሳጾችን

🌈 አባባሎችን
🌈 ትምህርቶችን ታገኙባቸዋላችሁ።
⚡በእውነት በረከታቸው አይለየን፤ በጸሎታቸው ይርዱን። አሜን!
🇬🇳 ጥር 8/5/2013

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-17 11:03:45 Watch "Watch "ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት የሰጠች ክብር ነጻነት" ለበለጠ ቻናላችንን #SUBSCRIBE , #Like #Share ያድርጉት እንላለን!" on YouTube


169 viewsMule negn, 08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 13:22:28 "በስመ ሥሉስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

#ጾም መድኃኒት ናት፡፡ አወሳሰድዋን በትክክል ላላወቁ ግን ጥቅም የላትም፡፡ ይህችን መድኃኒት የሚወስድ ሰው በየስንት ሰዓቱና በምን ያህል መጠን እንደምትወሰድ፣ ለምን ዓይነት በሽታ እንደምትጠቅም፣ በየትኛው አከባቢና የአየር ኹናቴ እንደምትወሰድ፣ ከእርሷ ጋር የሚኼዱና የማይኼዱ ምግቦችን እንዲሁም ከእርሷ ጋር የማይስማሙ ሌሎች ነገሮችን ለይቶ ማወቅ አለበት፡፡

እነዚህን ግምት ውስጥ አስገብቶ የማይወስዳት ሰው ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ታመዝንበታለች፡፡ አንድ በሐኪም የታዘዘልንን የደዌ ዘሥጋ መድኃኒት እንዲያሽለን ስንፈልግ በጥንቃቄ ልንወስደው ያስፈልጋል፤ የነፍሳችንን ደዌና በአእምሮአችን ውስጥ ያሉ ቁስሎችን ለመፈወስ ብለን በምንወስደው መድኃኒት ደግሞ ከዚህ የበለጠ መጠንቀቅ ይገባናል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ፣ ድርሳን 3፥8

ለበለጠ join
@ETHIOPIA_Hagerie

@Afe_Werk
175 viewsMule negn, 10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 17:51:56 +++ ወደ ሰማይ ባረገም ጊዜ እጁን ጭኖ ይባርክህ ዘንድ ራስህን ዘንበል አድርግ።
+++ ሁለንተናው እያበራ በመላእክት ዝማሬ እና ምስጋና ሲያርግም ወደላይ አንጋጠህ ተመልከት።
+++ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ እንዲያድርብህም ጥቂት ቀናት በኢየሩሳሌም ቆይ።

+++ ወንድሜ ሆይ በፍጹም ትጋት ሆነህ ይህን ሁሉ በልቡናህ አስብ።
+++ በእውነት ጌታህን ታየዋለህ።
+++ እርሱን ለማገልገል መከራን በሚቀበሉ ሰዎች አድሮ ያዘኑትን ደስ ለሚያሰኝ ጌታ ክብር ምስጋና ይግባው፤ ለዘላለሙ፡ አሜን።


= M.K.G

"ስሐ ኹሉም ነገር ክብር ለእግዚአብሔር ይኹን" አሜን።

ለበለጠ join
@ETHIOPIA_Hagerie

@Afe_Werk
177 viewsMule negn, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 17:51:51 በስመ ሥሉስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

እንዴት አላችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች።

ቸሩ አምላካችን ምስጋና ይድረሰው!

ቅዱስ ዮሐንስ ሳባ (አረጋዊ መንፈሳዊ) እንደጻፈው
ድርሳን 34

+ ወንድሜ ሆይ፡ ድንቅ ነገር እነግርህ ዘንድ እወዳለሁና ጸጥ ብለህ ስማኝ፡፡
+ አሳብህን ከመበታተን ሰብስበህ ስማኝ።
+ ልብህንም ከሥጋዊ ስሜት ለይ፡፡
+ እንዲህ የሆነ እንደሆነ በትሩፋት የተነገረውን ጸጋ ታገኛለህ፤ የዚህን ጸጋ መዓዛንም ታሸታለህ፡፡

+++ ሕፃናትን የፈጠረ ጌታ ትሕትናን የዕለት ጽንስ በመሆን እንደ ጀመረ እወቅ።
+++ ትህትናን ከእርሱ ተማር።
+++ ስላንተ የሠራውን ሥራ ሁሉ ታውቅ ዘንድ በትህትና ኑር፡፡
+++ በእርሱ አምሳል ይወልድህ ዘንድ በአንተ አምሳል ተወለደ፡፡
+++ በጨርቅ ተጠቀለለ፤ በተናቀ ቦታ በበረት አደረ።
+++ የሥጋ ብልጽግና እና የነፍስ ጸጋ መገኛ ሲሆን፡ ለዘላለም ነግሦ የሚኖር ንጉሠ ነገሥታት ጌታ በጨርቅ ተጠቀለለ ።

+++ የስደተኞች ማረፊያ የሚሆን እርሱን፡ እሽኮኮ ብለው ወደ ግብጽ አሸሹት።
+++ የሁሉ ደስታ የሚሆን ጌታን፡ ሄሮድስ ይገድለዋል ብለው እየፈሩ አሳደጉት፡፡
+++ መንግሥትን ሁሉ የሚሽር፤ መከራን የሚያሳልፍ እና ጸብ ክርክርን የሚያጠፋ
. እርሱን፡ የሞት ፍርድ እንደ ተፈረደበት ሰው ከአገር አስወጥተው ሰደዱት።
+++ ሞትን የሚያጠፋ እርሱ ሲሆን፡ እንገድለዋለን ከሚሉት ፊት ሸሸ።

+++ ከተለዩ የተለየ፡ ከከበሩት የከበረ ሲሆን፡ አንተን ያከብር ዘንድ በውኃ
. ተጠመቀ።
+++ ልዕልናውንም አብ በዮርዳኖስ “የምወደው ልጄ ይህ ነው” ብሎ ሲመሰክር ተሰማ።
+++ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ሲያርፍበት ታየ፡፡
+++ ይህም የሆነው ከአባቱ ጋር ያዋሕድህ ዘንድ አንተን ፈልጎ የመጣ እርሱ እንደሆነ ታውቅ ዘንድ፤ ከእርሱ ጋር በመኖርም በጎ ሥራ ብትሠራ ወደ አባቱ እንደሚያቀርብህ ትረዳ ዘንድ ነው።

+++ በትሩፋት መጋደልን እና ድል መንሳትን ያስተምርህም ዘንድ አርባ ቀን ጾመ።
+++ አንተ ቡሩክ ተብለህ ትመሰገን ዘንድ "የቡሩኩ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ"ብለው አይሁድ ዘበቱበት።
+++ በአጋንንት እጅ በኃጢአት በትር የተመታ የልቡናህን ራስ ያከብር ዘንድ ራሱን መቱት።

+++ የሰይጣንን ምክር ሰምታ የሚያሳዝን ኃጢአት የሰራች ሰውነትህን ጣዕም እንዲገኝባት ያደርጋት ዘንድ መራራ ከርቤን ጠጣ፡፡
+++ በዕፀ በለስ ምክንያት ከመጣ ሞት ያድንህ ዘንድ በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ፡፡
+++ ከመቃብር ያስነሳህ ዘንድ ወደ መቃብር ወረደ፤ ከጨለማ ወደ ብርሃን ያወጣህም ዘንድ ወደ ሲኦል ወረደ፡፡

+++ ይህን ሁሉ ላደረገልህ ጌታ አንተ የምተሰጠው ምንድነው?
+++ ጌታህን በማየት ደስ ይልህ ዘንድ ትወዳለህን?
+++ ከሆነ የእርሱን ነገር በመናገር የምታደንቅ ብቻ አትሁን፡፡
+++ እንደ ዮሐንስና እንደ ጴጥሮስ በዓይነ ሕሊናህ ተመልከተው እንጂ።
+++ ዘወትር ጌታህን በማሰብም ጸንተህ ኑር ።

+++ ይህን ካደረግህ፡ በእውነት ይገለጽልሀል፡፡
+++ የተወደደ ውብ መልኩን አይተህ ለማድነቅ ያበቃሀል።
+++ ነፍስህንም በበጎ ፍቅሩ ያቃጥላትል።
+++ በእርሱ ዘንድ ሞገስን ሰጥቶ ደስ ያሰኝሀል።

+++ እንደ እመቤታችን ማርያም በክንድህ እቀፈው።
+++ ሰውነትህም እንደ እመቤታችን የእርሱ ሞግዚት (አገልጋይ) ትሁን።
+++ ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) እጅ መንሻውን ይዘው ወደእርሱ በመጡ ጊዜ
. ከእነርሱ ጋር እጅ መንሻህን አቅርብለት።
+++ ከእረኞችም ጋር መወለዱን ስበክ (አውጅ)።
+++ ምስጋናውን ከመላእክት ጋራ ዘምር።

+++ ወደ ቤተ መቅደስም ባገቡት ጊዜ እንደ ስምዖን በክንድህ ታቀፈው።
+++ ወደ ግብጽም በወረደ ጊዜ እሽኮኮ ብለኸው ውረድ።
+++ አቅፈኸውም ከዮሴፍ ጋራ ሂድ፡፡
+++ እንደ ምድረ ግብጽ በረሃ የሆነች ነፍስህን እንደ ኢየሩሳሌም በጸጋ ያለመልማት ዘንድ።
+++ ጌታ ኢየሱስን ከሕፃናት ጋር ሲድህ: ሰርቀህ ሳመው።
+++ በመዓዛው ደስ ይላት እንደ ነበረች እንደመቤታችን፡ ሁሉንም ሕያው
. የሚያደርግ የጌታን መዓዛ አሽት።

+++ እንደ እመቤታችን ያቅፈው የነበረ፡ በመዓዛውም ደስ ይለው የነበረ አንድን ሰው አውቃለሁ።
+++ ሕፃናትን መስለህ፡ ጌታ በሕፃንነቱ ጊዜ በሄደበት ቦታ ሁሉ ተከተለው፡፡
+++ ይህን ካደረግህ፡ ፍቅሩ በአንተ ታድራለች።
+++ ከእርሱ ጋራ አንድ በመሆንህም ይዳሰስ ከነበረና ከሕያው ሥጋው ያለ መዓዛን ከሟቹ ሥጋህ ታሸታለህ፡፡

+++ ጌታ የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ሳለ፡ የአይሁድ መምህራን በጠየቁት ጊዜና እርሱም በመለሰላቸው ጊዜ የቃሉን ጥበብ ሰምተህ አድንቅ፡፡
+++ ለማጥመቅ ከዮሐንስ ጋራ በአንድነት ኑር።
+++ በዮርዳኖስ “የምወደው ልጄ ይህ ነው” የሚለውን የአባቱን ምስክርነት ስማ።
+++ መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ ሲቀመጥበት እይ፡፡
+++ በሚጾምበትም ጊዜ ከእርሱ ጋራ ጹም፡፡
+++ ውኃዉን ለውጦ ወይን ባደረገ ጊዜ ጋኖቹን ውኃ እየሞላህ ተመልከት፡፡

+++ ከውኃው ጉድጓድ አጠገብ ከሳምራዊቷ ጋራ በተቀመጠ ጊዜ ያስተማረውን ትምህርት ስማ።
+++ እግዚአብሔር አብ የሚወደውን እና በመንፈስ የሚደረገዉን ስግደት "የሚሰግዱለትም በመንፈስ ይሰግዱለታል" ብሎ ሲያስተምር ስማ፡፡
+++ ሙታንንም ባስነሳ ጊዜ ትንሣኤ እርሱ እንደሆነ ዕወቅ፡፡
+++ ኅብስቱንም ባበረከተ ጊዜ እንቅቡን ይዘህ ለተሰበሰቡት አድል።
+++ ወደገዳም በሔደ ጊዜ ሔደህ ሸኘው።
+++ በሚያስተምርበት ቦታ፤ በመርከብ ውስጥም፤ በበረሃም ከእርሱ ጋራ ኑር።

+++ ወደ ደብረ ዘይት ከእርሱ ጋር አብረህ ውጣ።
+++ በምኵራብም “እኔ ግን እላችኋለሁ…” እያለ ሲያስተምር ስማ።
+++ በኃጢአት ለሞተው ማንነትህ ሕይወትን ይሰጥ ዘንድ ከአልዓዛር ጋር ወደ መቃብር ግባ።
+++ እንደ ኃጢአተኛዪቱ ሴት በእንባህ እግሩን እጠበው፤ በጸጉርህም አብሰው (ሉቃ. 7፡ 38)፡፡
+++ “ኃጢአትህ ተሰርዮልሃል” ሲልህ ትሰማለህ።

+++ በማዕድ ጊዜም እንደ ዮሐንስ ባጠገቡ ተቀመጥ፡፡
+++ ኅብስቱን ባርኮ “ይህ ሥጋዬ ነው” ባለ ጊዜ ከእጁ ተቀበል።
+++ የደቀ መዛሙርቱን እግር ባጠበ ጊዜ ከኃጢአት ያነጻህ ዘንድ ቀርበህ እጠበኝ በለው፡፡
+++ የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነው ሰውነትህን ንጹሕ አድርገው፡፡
+++ ዘወትር እርሱን ለማመስገን የተጋህ ሁን፡፡

+++ በምግባር በሃይማኖትም ያጌጥህ ሁን፤ የመንፈስ ቅዱስን ነገር ለመማር የበቃህ ትሆን ዘንድ፡፡
+++ ከእርሱ ጋር መከራን ተቀበል፡፡
+++ ስለጌታህ ስድብን፤ መናቅን፤ የምራቅ መተፋትን እና በሚስማር መቸንከርን በጸጋ ተቀበል።

+++ ከእርሱ ጋር በመስቀል ተሰቀል፡ ከእርሱም ጋር ሙት፤ እርሱ እንደተነሣ ትነሣ ዘንድ (ሮሜ 6፡5)።
+++ ሰውነትህ (ነፍስህ) እንደ ማርያም መግደላዊት በፍርሀት ሁና ከመቃብሩ አጠገብ ትቁም።
+++ መላእክት “ምን ያስለቅስሻል?” ብለው ይጠይቋት ዘንድ።
+++ የምትወደውን ጌታ ባየችውም ጊዜ የአትክልት ጠባቂ መስሏት “ጌታዬን ወዴት ወሰድከው?” ብላ
እንደጠየቀችው ትጠይቀው ዘንድ (ዮሐ 20፡ 15)።
+++ ያን ጊዜ እንድታውቀው ሆኖ ያናግራታል።

+++ ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት በዝግ ቤት በገባ ጊዜ ተነሥተህ ተቀበለው።
+++ በጥብርያዶስ ባህር አጠገብ “ልጆች፡ አንዳች የሚበላ አላችሁን?” (ዮሐ 21፡5) ብሎ በጠየቀ ጊዜ ጴጥሮስን ምሰለው።
+++ መላእክት ያዘጋጁትንም ማዕድ ከእርሱ ጋር ተመገብ (ዮሐ. 21፡9)።
172 viewsMule negn, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 14:07:32 Watch "Watch "ቅዱሳን በሙሉ ከአምላክ አማልዱን" ከወደዱት #Like , #Share and #SUBSCRIBE ያድርጉት።" on YouTube


152 viewsMule negn, 11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ