Get Mystery Box with random crypto!

አንድ ሰው ቤቱን ሳይረከብ፣ የሱ የቱ እንደሆነ ሳያውቅ በፊት በካርታ ወይም በፕላን ላይ ያለን ቤ | የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች

አንድ ሰው ቤቱን ሳይረከብ፣ የሱ የቱ እንደሆነ ሳያውቅ በፊት በካርታ ወይም በፕላን ላይ ያለን ቤት መሸጥ አይፈቀድለትም። መልዕክተኛው ﷺ "ያንተ ያልሆነን ነገር አትሽጥ" ብለዋል።

105/ የተወሱልን ትርጉም እያወቀ በመልዕክተኛውም ﷺ ሆነ በተከበሩ ወራቶች ለመጥፎ ነገር ተወሱል የሚያደርግ (የሚመጀን) ሰው ይከፍራል።

106/ ሶላት ግዴታ ባይሆን ኖሮ! ብሎ የተመኘ ሰው ፍርዱ ምንድነው? ሸይኽ ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ፦ "ሶላትን ጠልቶ ከሆነ ይከፍራል፣ ነገር ግን በጣም ከመሳነፉ የተነሳ ከሆነ አይከፍርም"።

107/ ሸይኽ ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ፦ አንድ ሰው በፎቶው አማካኝነት የሰው ዓይን ሊበላው ይችላል። እናም የናንተንም ሆነ የቤተሰቦቻችሁን ፎቶ አታሰራጩ።

108/ የመልዕክተኛው ﷺ የቀብር አፈር እና የዘመዘም ውሃ መድሃኒቶች ናቸው። ሁለቱም ግን የሚበላለጡበት መንገድ አለ።

109/ መላኢካዎች በፈረስ ወይም በግመል ሊመሰሉ ይችላሉ። ነገር ግን መግደላችን ሱና በሚሆንልን እንስሳዎች አይመሰሉም።

110/ ፉቀሃዎች "እንስሳን በክብደት መሸጥ አይፈቀድም" ብለዋል።

111/ ቁርአን ላይ የጽፈትም ሆነ የድምፅ መቅጃ መሳሪያ የመሳሰሉትን ማስቀመጥ ሐራም ነው።

.......ይቀጥላል .......

#ምንጭ፦ ከክቡር ዶ/ር ሸይኽ ነቢል ሸሪፍ
አል-ሑሰይኒይ (ሐፊዘሁሏህ)
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh