Get Mystery Box with random crypto!

ከ̎ነ̎ብ̎ዩ̎ ﷺ̎ የተነገሩ ለሰው ልጅ መድሃኒት የሆኑ 30 ንግግሮች ================== | የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች

ከ̎ነ̎ብ̎ዩ̎ ﷺ̎ የተነገሩ ለሰው ልጅ መድሃኒት የሆኑ 30
ንግግሮች
===============================================================

1 " [ፀሐይ በመግቢዋ እስከምትወጣ ድረስ ወደ አላህ የተመለሰ (የተፀፀተ) አላህ ይቀበላዋል ]
.
2 " [እውቀትን ፈልጎ መንገድን የገባ ሰው፤ አላህ ወደ ጀነት የሚወስደውን መንገድ ያገራለታል]
.
3" [ከመልካም ነገር ምንንም አትናቅ፤ ወንድምህን
በፈገግታ ፊት መገናኘት እንኳን ቢሆን]
.
4" [ ከኔ አንድንም አንቀፅ ብትሆን አድርሱ]
.
5" [ ወደ መልካም የተጣራ የተከተሉት ሰዎች ምንዳ ሳይቀነስ የነሱንም ምንዳ ለሱ ይሆንለታል ፤ ወደ ጥመት የተጣራ የተከተሉት ሰዎች ወንጅል ሳይቀነስ የነሱን ወንጀልም በሱ ላይ ይሆናል]
.
6" [ ከእናንተ መካከል መጥፎን ነገር ያየ በእጁ ይቀይር፣ ያልቻለ በምላሱ ፣ ያልቻለ በልቡ , ይህም የእምነት ደካማው ደረጃ ነው]
.
7" [ ከእናንተ በላጫችሁ ቁርአን የተማረና ያስተማረ ነው]
.
8" [ ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለው እስካላመናችሁ ጀነት አትገቡም፣ እስካልተዋደዳችሁ ድረስ አታምኑም ።
ብትሰሩት የምትዋደዱበት የሆነን ነገር ላመላክታችሁን? በመካከላችሁ ሰላምታን አብዙ ]
.
9" [ ከተቸገረ ሰው ላይ ችግሩን ያቀለለ አላህ በዱንያም በአኼራም ያቀለለታል ]
.
10" [ ሲሸጥ ፣ ሲገዛ ሆነ ሲፈርድ ይቅር ያለ አላህ
ይዘንለት]
.
11" አንድ ባሪያ አንድን ባሪያ በዱንያ ላይ ገመናውን አይደብቅለትም አላህ በአኼራ የደበቀለት ቢሆን እጂ]
.
12" [ ዝምድና ከዓርሽ ተንጠልጥላ፥ የቀጠለኝ አላህ ይቀጥለው የቆረጠኝ አላህ ይቁረጠው ;ትላለች]
.
13 " [ በእውነት ላይ አደራ ፤ እውነት ወደ መልካም
ይመራል መልካምም ወደ ጀነት ይመራል ]
.
14" [ እኔና የቲሞችን የሚንከባከብ በጀነት ውስጥ
እንደዚህ ነን ፥ -መካከለኛዋን እና ጠቋሚ ጣታቸውን አጣምረው እያመላከቱ]
.
15 "[ እሱ የሚወሳበትን የአላህን ቤት ያስገነባ ሰው አላህ ለሱ በጀነት ውስጥ ቤትን ይገነባለታል]
.
16 "[ ህዝቦቼን አስቸግራለሁ ብየ ባልሰጋ ኖሮ፥ ከሁሉም ሰላት (በፊት) በሲዋክ ባዘዝኳቸው ነበር]
.
17 "[ ሁለት ብርዳማ ሳላቶችን የሰገደ ጀነት ገባ ;
(የፈጅር እና ዓስር ሰላት)]
.
18 "[ አንድ ሰው ወንጀል ሰርቶ;ከዚያም ታጥቦ ሰላት ሰግዶ ምህረትን አይጠይቅም ምህረት የተደረገለት ቢሆን እንጂ]
.
19 " [ አንድ ባሪያ ለአላህ ብሎ አንድ ቀን አይፆምም አላህ ሰባ አመታትን ከጀሃነም ያራቀው ቢሆን እንጂ]
.
20" [ ምፅዋት ስህተትን ታጠፋለች ውሃ እሳትን
እንደምታጠፋው]
.
21" [ ከዑምራ እስከ ዑምራ በመካከላቸው ያለውን
ያስምራል; 'ትክክለኛ' ሐጅም ምንዳው ጀነት ነው]
.
22 " [በሁለት እግሮቹና በሁለት ፂሞቹ (ከንፈሮቹ) መካከል ያሉትን ዋስትና የሚሰጠኝ ጀነትን ዋስትና እስጠዋለው]
.
23 " [ አንድ ሰው የተጠማን ውሻ አይቶ ከመጣማቱ የተነሳ አፈር ሲልስ ተመልክቶ በጫማው ውሃ በመቅዳት አጠጣው አላህም ስራውን ወደደለት ጀነትም አስገባው]
.
24 " [ ሴት ልጅ አምስት ወቅት ሰላቷን ከሰገደች ፣
ረመዳንን ከፆመች ብለቷን ከጠበቀችና ባሏን ከታዘዘች በፈለገችበት የጀነት በር ግቢ ትባላለች]
.
25 " ከልቡ 'ላ ኢላሃ ኢለላህ ' (ከአላህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ) ያለ ጀነት ገባ]
.
26 " [በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር ፤ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ ጎረቤቱን ያክብር ፤ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምን ይናገር አልያም ዝም ይበል ]
.
27 "[ ከሰዎች ሁሉ በላጩ ይበልጥ ለሰዎች ጠቃሚው ነው]
.
28 " [ በማንኛውም ሁኔታ ላይ ሆነህ አላህን ፍራ፥
ከመጥፎ ስራ በኃላም መልካምን አስከትል ታብሳታለች ፤ ሰዎችንም በመልካም ስነምግባር ተኗኗር]

29" [ጀግና ማለት ታግሎ የጣለ ሳይሆን በቁጣ ጊዜ ነፍሱን የሚቆጣጠር ነው ]
.
30 " [ በኔ ላይ አንድን ሰላት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስርን ያወርዳል ]
https://t.me/Adnan567mh