Get Mystery Box with random crypto!

بسم الله الرحمن الرحيم ከየትኛውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ የሰሞነኛወቹ የባለ | በሚጠቅምህ ነገር ላይ ብቻ መሽሁል ሁን!!

بسم الله الرحمن الرحيم

ከየትኛውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ የሰሞነኛወቹ የባለ ድብቆቹ ሚስጥረ ስላሴወች ችኩል ሆነው ይታያሉ
==========================
ባገኙት ነገር ላይ ሁሉ ያለ ዕዉቀት ያለ መረጃ ሁሉ ጥልቅ የሚሉ "እንደ እርጎ ዝንብ " በጣም የበዙ ናቸዉ።
==========================
ይባስ ብሎም በሰለፊይ ሲሆን በጣም ያሳዝናል።መረጋጋት፣ ነገሮችን ማጣራት የለም፣በእውቀትና በመረጃ መጓዝ ሳይሆን ያለ በቂ እውቀት፣ ያለ ደረጃና ያለ ቦታው ባገኙት ርዕስ ሁሉ ላይ መግባት የተለመደ ነገር ሆኗል።
==========================
ነገሮችን ማንቦጫረቅ፣ፈተናን ማባባስ ችሎታና ተቆርቋሪነት፣ ብቃትና ክፉን ተከላካይነት ተደርጎ እየተጨበጨበለት ይታያል ይሰማልም።


ሸህ ኢብኑ ዑሰይሚን الله ይዘንለትና ቀጣዩን ብሏል

እርጋታ ማለት በነገሮች ላይ
ኣለመቻኮል ማለት ነው። አብዛኛው ሰው እየጠፋና እየተዋረደበት ያለውም በነገሮች ላይ ችኩል ከመሆኑ የተነሳ ነው። ይህም ወሬዎችን በማቀባበሉ እንዲሁም አንድን ነገር እንደሰማ ፍርድ በመስጠቱና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ በመጣደፉ ነው። አንዳንዱ ሰው አንድን ወሬ እንደሰማ (እርግጠኛ ሆኖ) ወዲያው ያወራል። ያስተላልፋል። አንዳንዱ ደግሞ ፍርድ ለመስጠት ይቻኮላል። የሆነ ነገር ስለ አንድ ግለሰብ ይሰማና በቃ ይህንን ነገር ያ ግለሰብ ተናግሯል ወይም አድርጎታል ብሎ በእርግጠኝነት ፍርድ ለመስጠት ይጣደፋል። ከዚያም ያ ሰው ተሳስቷል… ያ ሰው ጠምሟል… እና የመሳሰሉትን በመለጣጠፍ ፍርድ ይሰጣል። ይህ ግን ስህተት ነው። ስለዚህም እርጋታ በሁሉም ነገር ላይ መልካም ነው።

(ሸርሁ ሪያዱ-ሳሊሂን: 3/577-578)

yewesejiw

@Abu_babelheyr_bin_Sadik